አቡነ ማትያስ (አባ ተክለማርያም አስራት)
H E Abune Matiyas
ማሳሰቢያ፦ ይህ ጽሑፍ በመጀመሪያ ዋሽንግተን ዲ.ሲ. ለሚገኘው የነፃነት ለኢትዮጵያ ራድዮ የተላከው በእኔ ሥም ቢሆንም፣ በኀብረት ያዘጋጀነው ግን ጉዳዩ የከነከነንና ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም አካባቢዎች የምንገኝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ከርስቲያን ምዕመናን(ት) ነን፤ ስለሆነም፣ ይህ ዘገባ የተዘጋጀው በኢትዮጵያ፣ በታላቋ ብሪታንያ፣ በጀርመን፤ በእሥራኤል፣ በስዊትዘርላንድና በዩ. ኤስ. አሜሪካ ከሚገኙ የመረጃ ምንጮች ጋር በመተባበር ነው፡፡ በዘገባው ውስጥ የተካተቱት ጉዳዮች ሁሉ በአዲስ አበባዎቹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ በደህንነት ጥበቃው መ/ቤትና በጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት፣ እንደዚሁም ደግሞ ቀደም ብለው በተጠቀሱት ስድስት ሀገሮች ውስጥ ከሚኙት የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች በተጨማሪ፣ በኢየሩሳሌሙ የመንበረ ጳጳስ ግቢ ቤተ መዘክርና በቆንስላው ጽ/ቤት በሥርዓት ተመዝግበው የተቀመጡ ናቸው፤ በኢየሩሳለሙ የመንበረ ጳጳስ ግቢ የነበረውን ማስረጃ ለማጥፋት አቡነ ማትያስ ዕድል ተሰጥቷቸው ነበር ቢባል እንኳን፣ በለሎቹ ዘንድ ያሉትን ሊደርሱባቸው ካለመቻላቸውም በላይ በህይወት ያሉ የቃል ምሥክሮችም ጥቂት አለመሆናቸው ሊታወቅ ይገባል። (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
ethioforem
No comments:
Post a Comment