Sunday, June 30, 2013

በድጋሚ የወጣ የአቋም መግለጫ፤ ድምጼን ከፍ አድርጌ እደግመዋለሁ!

June30,2013
 
አቤ ቶኪቻው
በኬኒያ የስደት “ኬዝ” ጋገራእኔ ኦሮሞ ነኝ፡፡ ኦሮሞነቴን የሰጡኝ አባቴ እና እናቴ ናቸው እንጂ ከሱፐር ማርኬት ገዝቼው አይደለም፡፡ እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ኢትዮጵያዊነቴን ያገኘሁት ከእናት እና ከአባቴ እንጂ አንዳች አካል እላዬ ላይ ለጥፎብኝ አይደለም፡፡ በኢትዮጵያዊነቴ እንደምኮራው ሁሉ ኦሮሞነቴም ኩራቴ ነው፡፡
በኢትዮጵያ በርካታ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተዟዙሪያለሁ፡፡ የዛን ጊዜ ከ”አካም ቡልተኒ” ውጪ ምንም ኦሮምኛ አላውቅም ነበር፡፡ ነገር ግን በየባላገሩ ያሉ ኦሮሞዎች የኔ አማርኛ ተናጋሪ መሆን፤ ወይም ኦሮምኛ ቋንቋ አለመቻል አንድም ቀን አሳስቧቸው አያውቅም፡፡ ሰው በመሆኔ ብቻ አክብረው እርጎ አቅርበውልኝ፣ እርጎ የሆነ ፈገግታ ለግሰውኝ፣ ለራቸው ከሚተኙበት የተሸለ መኝታ ሰጥውኝ በእንክብካቤ ነው የሚያስተናገዱኝ፡፡
አንዳንዶች፤ ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ አልመሆኑን ሊነገሩኝ ታሪክ እንዳነብ፣ አዋቂ እንድጠይቅ፣ ጸሎት እንዳደርግ ሁላ መክረውኛል፡፡ እኔ ግን ይሄንን ሁሉ ማድረግ ሳያስፈልገኝ ከኦሮሞ የሚፎካከር ኢትዮጵያዊ እንደሌለ አሁን በቅርቡ የዞርኩባቸው የኦሮሚያ ገበሪዎች አረጋግጠውልኛል፡፡ ይህንን ነገር እኔ ብቻ ሳልሆን በቅርብ የኦሮሞን ህዝብ ጠንቅቀው የሚያውቁት እነ ጀነራል ከማል ገልቹ አረጋግጠውታል፡፡ እነ አቶ ቡልቻ ደመቅሳም መርቀውታል፡፡ ለዛም ነው ዛሬ የጀነራል ከማል ገልቹ ኦነግ በስፋት ተቀባይነት እያገኝ የመጣው፡፡ ለዛም ነው ዛሬ የኦሮሞ ልጆች በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ያሸበረቀ የኦነግ አርማን  ከአረንጓዴ ቢጫ ቀዩ የሀገራቸው ባንዲራ ጋር ጎን ለጎን ይዘው በአደባባይ ስለ ኢትዮጵያ ልጆች የሚጮሁት!
ለብቻ መኖር የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ቢሆን ኖሮ እንደ ኦሮሞ ህዝብ ጀግንነት እና ብዛት፤ ጮክ ብዬ እደግመዋለሁ እንደ ኦሮሞ ህዝብ ጀግነነት እና ብዛት፤  አርባ አመት ፈጅቶ አይኮላሽም ነበር፡፡
በአሁኑ ጊዜ የኦሮሞ ህዝብ እየተበደለ እንደሆነ ምንም ጥያቄ የለውም፡፡ በርካታ ወዳጆቼ ኦሮምኛ ተናጋሪ ስለሆኑ ብቻ ኦነግ ናችሁ ተብለው ከዩንቨርስቲ ወጥተው እስር ቤት ገብተዋል፡፡ ከስራቸው ተባረው ለስደት ተዳርገዋል፡፡ ወዘተ ተደርገው ወዘተ ሆነዋል፡፡ ልክ እንደዛ ሁሉ ግን በደሉ ሌሎችም ዘንድ አለ፡፡ አማራውም ትግሬውም አዲሳቤውም ሁሉም ቁስል አለበት፡፡
አብሮ ታክሞ አብሮ መኖር ለሁሉም ይበጃል!!!

ከፌዴራል መንግሥት በጀት በሕግ በተቀመጡ መመዘኛዎች መሠረት ከተመደበው 20 ሚሊዮን ብር ውስጥ፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባት ሚሊዮን ብር ሕግን በመጣስ ኢሕአዴግ ለመረጣቸው ፓርቲዎች አከፋፍሏል በሚል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄ ቀረበበት፡፡

ከፌዴራል መንግሥት በጀት በሕግ በተቀመጡ መመዘኛዎች መሠረት ከተመደበው 20 ሚሊዮን ብር ውስጥ፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባት ሚሊዮን ብር ሕግን በመጣስ ኢሕአዴግ ለመረጣቸው ፓርቲዎች አከፋፍሏል በሚል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄ ቀረበበት፡፡




ምርጫ ቦርድ ሕግ በመጣስ በኢሕአዴግ ለተመረጡ ፓርቲዎች ገንዘብ ሰጥቷል በሚል ጥያቄ ቀረበበ

“ፓርቲዎች ከዜጎች ገንዘብ እየተቀበሉ የቪዛ የድጋፍ ደብዳቤ ሲሰጡ ቦርዱ ችላ ብሏል” አቶ ግርማ ሰይፉ
“ሆደ ሰፊ የሆንነው ዴሞክራሲ እንዲጎለብት በማሰብ ነው” 
ፕሮፌሰር መርጋ በቃና
ከፌዴራል መንግሥት በጀት በሕግ በተቀመጡ መመዘኛዎች መሠረት ከተመደበው 20 ሚሊዮን ብር ውስጥ፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባት ሚሊዮን ብር ሕግን በመጣስ ኢሕአዴግ ለመረጣቸው ፓርቲዎች አከፋፍሏል በሚል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄ ቀረበበት፡፡
በምርጫ ለሚሳተፉ ፓርቲዎች ሥራ ማስፈጸሚያና ለዕለት ተዕለት ተግባራት ማከናወኛ በጀት የማከፋፈል ሥልጣን የተሰጠው የምርጫ ቦርድ አመራሮች ለቀረበላቸው የሕግ ጥሰት ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጡ አልፈውታል፡፡ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የሥራ አመራሮች የ2005 ዓ.ም. አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ባለፈው ሐሙስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት፣ በተጠቀሰው የሕግ ጥሰትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠይቀዋል፡፡
የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና በዓመቱ ውስጥ የተካሄዱት የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤቶችና የአካባቢ ምርጫዎች ዴሞክራሲያዊና ነፃ ሆነው መጠናቀቃቸውን፣ ለዚህም ውጤት ቦርዱ ያከናወናቸውን ዝርዝር ተግባራት በ14 ገጽ ሪፖርታቸው ጨምቀው አቅርበዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይም በክልል ምክር ቤቶች መቀመጫ ላላቸው አሥር የፖለቲካ ፓርቲዎች ለዕለት ከዕለት ተግባር ማከናወኛ በጀት 20 ሚሊዮን ብር ከመንግሥት በማስፈቀድ ባላቸው መቀመጫ ብዛት ተሰልቶ የባንክ ሒሳብ ቁጥራቸውን ላሳወቁ ስምንት የፖለቲካ ፓርቲዎች ማከፋፈሉን የቦርዱ ሪፖርት ያስረዳል፡፡ ይሁን እንጂ ከተጠቀሰው 20 ሚሊዮን ብር የትኛው ፓርቲ ምን ያህል እንዳገኘ አልተካተተም፡፡
ሪፖርቱ ከቀረበ በኋላ በምክር ቤቱ ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ለፓርቲዎች የሚከፋፈል የመደበው 20 ሚሊዮን ብር በጀት ላይ ጠንከር ያለ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ከተጠቀሰው 20 ሚሊዮን ብር የትኛው ፓርቲ ምን ያህል ወሰደ የሚል ጥያቄ ማንሳት እንደማይፈልጉ፣ ምክንያቱ ደግሞ መመዘኛው በሕግ የተቀመጠና ቦርዱን የሚመለከት ባለመሆኑ እንደሆነ፣ ነገር ግን በመመዘኛው መሠረት ኢሕአዴግና አጋሮቹ አብዛኛውን እንደወሰዱት ግልጽ መሆኑን በመጠቆም ነበር አቶ ግርማ ወደ ጥያቄያቸው የገቡት፡፡
በመመዘኛው መሠረት ኢሕአዴግ ካገኘው ገንዘብ ውስጥ ሰባት ሚሊዮን ብር የሚሆነውን በራሱ ፍላጎት ለመረጣቸው ፓርቲዎች እንዲከፋፈልለት በመጠየቅ ለቦርዱ መመለሱንና ቦርዱም በኢሕአዴግ ለተጠቆሙት ፓርቲዎች ማከፋፈሉን አቶ ግርማ ገልጸዋል፡፡ ጥያቄያቸውም ያጠነጠነው በዚህ ላይ ነው፡፡
“የተጠቀሰው ሰባት ሚሊዮን ብር በሕግ መሠረት ለተፈለገው ዓላማ ነው ወይ የዋለው?” በሚል ጠንከር ያለ ድምፀት ጥያቄያቸውን ያነሱት አቶ ግርማ፣ “በመጀመሪያ ደረጃ በምክር ቤት ወንበር ለሌላቸው ፓርቲዎች የመንግሥትን ገንዘብ የማደል ሥልጣን ለኢሕአዴግ ማን ሰጠው?” በማለት አክለዋል፡፡ በመቀጠልም ገንዘቡን ኢሕአዴግ ሳይሆን ያደለው ምርጫ ቦርድ መሆኑ እንዳስገረማቸው፣ “ኢሕአዴግ እገሌ እገሌ ለሚባሉት ፓርቲዎች ስጡልኝ ብሎ በጠየቀው መሠረት ገንዘቡን ለተባሉት ፓርቲዎች ያደለው ምርጫ ቦርድ ነው፤” ብለዋል፡፡
ይህንኑ ጉዳይ በወቅቱ የቦርዱን ሰብሳቢ በአካል አግኝተዋቸው እንዴት ይህንን ታደርጋላችሁ የሚል ጥያቄ አንስተው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ግርማ፣ ሰብሳቢው ፕሮፌሰር መርጋ በቃና በወቅቱ ምን ክፋት አለው የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው በይፋ ተናግረዋል፡፡ “በእርግጥ በቅን ልቦና ስናስበው ምንም ክፋት የለውም፡፡ በሕግ ግን አይቻልም፡፡ በሕግ ላልተፈቀደላቸው ፓርቲዎች ምርጫ ቦርድ ገንዘብ ማደል አልተፈቀደለትም፤” በማለት፣ “በየትኛው ሥልጣናችሁ ገንዘቡን እንዳደላችሁ ያስረዱን፤” ሲሉ ፕሮፌሰር በቃናን በምክር ቤቱ ፊት ጠይቀዋል፡፡
ባነሱት የሕግ ጥሰት ጉዳይ ላይ የበለጠ ማስረዳት የመረጡት አቶ ግርማ፣ “በምሳሌ ላስረዳዎት፤ መንገዶች ባለሥልጣን የተፈቀደለትን በጀት መጨረስ ስላልቻለ ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መስጠት አይችልም፤” ሲሉ የሕግ ጥሰቱን ለማሳየት ሞክረዋል፡፡
ከተጠቀሰው በመንግሥት ለፓርቲዎች የተፈቀደ 20 ሚሊዮን ብር በጀት ውስጥ ኢሕአዴግ በአከራካሪዎቹ መስፈርቶች ያገኘው ገንዘብ ግዙፍ ስለሆነበት ለሌሎች ፓርቲዎች እንዲከፋፈልለት ማድረግ እንደማይችል ገንዘቡን የማይፈልገው ከሆነ በሕግ አግባብ ማድረግ የሚችለው ለምርጫ ቦርድ መመለስ ብቻ ነው በማለት አስረድተዋል፡፡
“የእኔ ፓርቲ ከ20 ሚሊዮን ብር ውስጥ ለዓመት ሥራ ማስኬጃ የደረሰው ሦስት ሺሕ ብር ነው፡፡ እኛ ስለማይበቃን ገንዘቡን እንደመለስነው ኢሕአዴግም ይህንን ነበር ማድረግ ያለበት፤” ብለዋል፡፡ በማከልም ይህ ስህተት ሊታረም ይገባል ብለው፣ የሚታረመው ሌሎች ምክንያቶችን በመደርደር ሳይሆን ኢሕአዴግ ከሌላ የገንዘብ ምንጩ የተከፋፈለውን ገንዘብ ለምርጫ ቦርድ በመመለስ ብቻ ነው በማለት ተከራክረዋል፡፡
ከዚህ በተለየ ጉዳይ ጥያቄያቸውን ለምርጫ ቦርድ አመራሮች ማቅረባቸውን በመቀጠል፣ የመደራጀት መብት በአገሪቱ ስላለ ብቻ የፖለቲካ ፓርቲ እየመሠረቱ ነገር ግን ለፖለቲካ ተልዕኮ ሳይሆን ለሕገወጥ የገንዘብ መሰብሰቢያነት የሚጠቀሙ ፓርቲዎች መኖራቸው በግልጽ እየታወቀ፣ ቦርዱ ቸልተኝነትን መርጧል በማለት፣ “ሥራችሁ ምንድን ነው? ምንድን ነው የምታደርጉት?” ሲሉ አቶ ግርማ ጠይቀዋል፡፡ “በአሁኑ ወቅት ንግድ ፈቃድ ከማውጣት የፖለቲካ ፓርቲ ፈቃድ ማውጣት ይቀላል የተባለው እውነት እየሆነ ነው፡፡ ነገር ግን ንግድ ፈቃድ ያወጡ ግለሰቦች ፈቃዱን ካልተጠቀሙበት ይሰረዛሉ፤” የሚሉት አቶ ግርማ፣ “ፓርቲዎች ምን ሲያደርጉ ነው እዚህ አገር የሚሰረዙት?” በማለት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ለዚህ ጥያቄያቸው ራሳቸው የሰጡት ምላሽ፣ የፖለቲካ ፓርቲ ፈቃድ ያላቸው ድርጅቶች ከፖለቲካ ዓላማ ይልቅ ከዜጎች ገንዘብ እየተቀበሉ የውጭ አገር የቪዛ ማስመቻ ድጋፍ ደብዳቤ በመጻፍ ዜጎችን ለስደት እየዳረጉ ነው የሚል ነው፡፡ “መንግሥት ለፓርቲዎች የሰጠውን የመንግሥት ቤት ለሌላ ሦስተኛ ወገን አከራይተው በጥቅም ሲጣሉ በሚዲያ እየተሰማ ቦርዱ ግን ዝምታን መርጧል፤” ሲሉ ተጨማሪ ወቀሳ ሰንዝረዋል፡፡
ለቀረቡት ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት የጀመሩት ፕሮፌሰር መርጋ በቃና፣ ለፓርቲዎች ተብሎ ከመንግሥት የሚመደበውን የድጎማ ገንዘብ ቦርዱ የሚያከፋፍለው ሕግን መሠረት አድርጎ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በሕጉ መሠረትም ፓርቲዎቹ በፌዴራልም ሆነ በክልል ምክር ቤቶች ውስጥ ያላቸው መቀመጫ ብዛት አንደኛው መስፈርት መሆኑን፣ የሌሎቹ ፓርቲዎች ለቅስቀሳ ዘመቻ የሚያስፈልጋቸውን ወጪ በገንዘብና በዓይነት የሚሸፈን እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
በዚህ መስፈርት መሠረት ተጠቃሚ መሆን የሚገባቸው አሥር ፓርቲዎች እንደነበሩ፣ ከእነዚህ ውስጥ ለስምንቱ መከፋፈሉን ሁለቱ ግን የገንዘቡ መጠን ስላነሰባቸው አለመቀበላቸውን ገልጸው፣ “ገንዘቡን የወሰዱ ፓርቲዎች በምን ላይ እንዳዋሉት ኦዲት አስደርገው ማቅረብ አለባቸው፤” ብለዋል፡፡ ከዚህ ባለፈ ቦርዱ በኢሕአዴግ ጠቋሚነት በሕጉ መሠረት ለማይገባቸው ፓርቲዎች አከፋፍሏል ለሚለው ጥያቄ ምላሽ አልሰጡም፡፡
ፓርቲዎች ሕግን እንዲያከብሩ በተደጋጋሚ እየመከሩ መሆኑን የሚገልጹት ፕሮፌሰር መርጋ፣ “ሕጉ ሙሉ ለሙሉ ቢከበር ለቦርዱም ሥራ ቀለለለት ማለት ነው፡፡ ነገር ግን በሆደ ሰፊነት ነው የምንሠራው፡፡ ምክንያቱም ለዴሞክራሲና ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓት መጎልበት ሲባል፤” ብለዋል፡፡
ቦርዱ በዚሁ ሁኔታ ይቀጥላል ማለት እንዳልሆነ የጠቆሙት ሰብሳቢው ሕግን ማክበር በማይችሉ ላይ ዕርምጃ ይወስዳል ብለዋል፡፡ “ለምሳሌ አራት ፓርቲዎች ፈቃድ ከወሰዱ በኋላ ከቦርዱ ጋር ግንኙነት በማቋረጣቸውና በተደጋጋሚ በሚዲያ ጥሪ ቢተላለፍላቸውም ባለመገኘታቸው ተሰርዘዋል፤” የሚሉት ፕሮፌሰር መርጋ፣ በአሁኑ ወቅት ፈቃድ ካላቸው 76 ፓርቲዎች ውስጥ 22 የሚሆኑት ሕጉን ሙሉ ለሙሉ ያሟሉ መሆናቸውን፣ የተቀሩት ግን በከፊል ማሟላታቸውንና ከእነዚህ ጋር በቀጣይ ሕግ የማስከበር ሥራን በመወያየት እንደሚያከናውኑ አብራርተዋል፡፡
source: Ethiopia Reporter

የኢህአዳግ ታንክና ባንክ


ግርማ ሠይፉ ማሩ
ይህንን ርዕስ የወሰዴኩት አቶ ገብሩ ገብረማሪያማ የኦሮሞ ፌዳራሉስት ኮንግረስ አባሌ ከኢሳት ጋር ባቀረቡት ቃሇ መሌሌስ መነሻ ነው፡፡ የምርጫ ቦርዴ ሇምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት መነሻ አንዴ አንዴ የምክር ቤት አባሊት የሰጠሁትን አስተያየት መሰረት አዴርገው ከጠርዝ የወጣ አስተያየት ሲሰጡ ነበር፡፡ ከነዚህ አስተያየቶች ዋነኛው የነበረው በቅርቡ በተካሄዯው በእነርሱ ፍትሃዊና ትክክሇኛ በእኛ ፌክ ምርጫ ተቃዋሚዎች ያሌተሳተፉት የእናቴ ቀሚስ አዯናቀፈኝ በሚሌ ነው፡፡ የሚሌ የነበረ ሲሆን ከአቶ ገብሩ አሰተያየት ጋር ስሇገጠመሌኝ ሌዋሰው ወዯዴኩ፡፡
Read more: http://www.ethiomedia.com/abc_text/eprdf_tank_and_bank.pdf

Norway must react to U.S. surveillance


 The Monitoring scandal in the United States is a serious threat to privacy, says Liberal leader Trine Skei Grande. The Liberal  party demands that the government respond to the possible surveillance of Norwegian citizens. The monitoring scandal  that has been revealed in the last month, can be dangerous for democracy and should not be tolerated by the Norwegian authorities according to Skei Grande.
 The fight against Prism monitoring must take place on two fronts, through sanctions against U.S. authorities and public international law, she said. The monitoring program has provided U.S. authorities access to information about individuals outside the United States, provided by companies like Apple, Google and Facebook. This information may also have been shared with PST in Norway, reported Klasse Kampen Friday. Liberals are concerned that this information is collected about individuals can be abused and will  not work to improve privacy on the Internet.
 
 
Source: NTB scanpix / Photo Wikipeda / Norway Today









ESAT Weekly News 30 June 2013


የውጭጉዳይ ሚ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም አሁንም በስብሰባ ላይ ሲዋረዱ የሚያሳይ ቪድዮ ይመልከቱ


የአርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ከአገር እንዳይወጡ ታገዱ

6dfc868ecccfc66f6592d0a6b7e266ba_XL
30 June 2013
ፍርድ ቤት ቀርበው በ25 ሺሕ ብር ዋስ ተለቀቁ
የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ፣ ተጠርጥረው በተከሰሱበት ከፍተኛ የማታለል ወንጀል ምክንያት ከአገር እንዳይወጡ ሰኔ 21 ቀን 2005 ዓ.ም. የእግድ ትዕዛዝ ተላለፈባቸው፡፡
ቀደም ባለው ቀጠሮ ሳይቀርቡ በመቅረታቸው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አምስተኛ ወንጀል ችሎት ለሰኔ 21 ቀን 2005 ዓ.ም. ታስረው እንዲቀርቡ ባዘዘው መሠረት ሰኔ 21 ቀን 2005 ዓ.ም. የቀረቡ ሲሆን፣ በመጀመርያ ቀጠሮ ያልቀረቡበት ምክንያታቸውን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡
በሕመም ምክንያት ሊቀርቡ አለመቻላቸውንና በዕለቱም በሕመም ላይ መሆናቸውን ለችሎቱ አስረድተዋል፡፡ ሰኔ 11 ቀን 2005 ዓ.ም. ተጠርጣሪዎቹ የተመሠረተባቸው ክስ ተሰምቶ የእምነት ክህደት ቃላቸውን መስጠት ቢገባቸውም፣ ዓቃቤ ሕግ ከክሱ ጋር የሚያያይዘው ቀሪ ማስረጃ እንዳለው ገልጾ፣ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጠው በመጠየቁ ክሱ ሳይሰማ ቀርቷል፡፡
ሌላው ዓቃቤ ሕግ ለችሎቱ ያመለከተው ጉዳይ ተጠርጣሪዎቹ በአርበኞች ማኅበር ሠራተኞች ላይ ዛቻና ማስፈራራት እያደረሱ መሆኑን፣ ፕሬዚዳንቱ ቢሮ ባይገቡም ቤታቸው ውስጥ ሆነው እየሠሩ መሆናቸውን፣ በዚህ ሁኔታ ከቀጠሉ የማኅበሩ ንብረቶች አደጋ ላይ መሆናቸውን በማስረዳት፣ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥለት ጠይቋል፡፡
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆችም ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ማመልከቻ በማስረጃ የተደገፈ መሆኑን ለችሎቱ በመግለጽ፣ የዓቃቤ ሕግ አቤቱታ ተዓማኒነት እንደሚጐድለው በማስረዳት አቤቱታው ውድቅ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል፡፡ ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄም በቤታቸው መሥራታቸው ለመታመማቸው ማስረጃ እንደሆነም አመልክተዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ድብደባ፣ ማስፈራሪያና ዛቻ እየደረሰባቸው ስላሉት የማኅበሩ ሠራተኞችና የዓቃቤ ሕግ ምስክሮችን በሚመለከት ዓቃቤ ሕግ በማስረጃ የተደገፈ አቤቱታ በጽሕፈት ቤት በኩል እንዲያቀርብ በማሳሰብ፣ ፕሬዚዳንቱ በ25 ሺሕ ብር ዋስ እንዲለቀቁ አዟል፡፡ ክስ ለመስማትና የእምነት ክህደት ቃል ለመቀበል ለሐምሌ 4 ቀን 2005 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በከፍተኛ ሙስና የተዘፈቀው መከላከያ ሂሳቡ እንዳይመረመር ታዘዘ

-የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በሚያዚያ ወር 2005 ዓ.ም ባቀረበው ሪፖርት የመከላከያና የደህንነት ተቋማት
የፋይናንስ አያያዝ ከፍተኛ ችግር እንዳለበት ማመልከቱን ተከትሎ በየመ/ቤቶቹ የተነሳውን ቅሬታ ለመፍታት በቀጥታ
እነዚህን ተቋማት በተለየ ሁኔታ ኦዲት ለማድረግ የሚያስችል አዋጅ እየተረቀቀ መሆኑ ተጠቆመ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር አቶ ገመቹ ዱቢሶ ሚያዚያ 22 ቀን 2005 ዓ.ም ለፓርላማው ባቀረቡት የ2004 ዓ.ም
የፌዴራል የመንግስት መ/ቤቶች የሂሳብ አያያዝ ሪፖርት በተለይ በዘጠኝ መ/ቤቶች 3 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር
ባልተሟላ ሰነድ ወጪ ሆኖ መገኘቱን፤ ከዚህ ውስጥ 3 ነጥብ 2 ቢሊየን ብሩ የመከላከያ ሚኒስቴር መሆኑን
መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
እነዚህ ተቋማት ላወጡት ገንዘብ ትክክለኛ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ተጠይቀውም ማቅረብ አለመቻላቸውን ለፓርላማው
ሪፖርት ካደረጉ በኋላ በተለይ የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈረጌሳን ጨምሮ የተለያዩ ሹማምንት ሪፖርቱን
በአደባባይ እስከማብጠልጠል የደረሰ ትችት ሲያቀርቡ ተደምጠዋል፡፡ ዋናው መከራከሪያቸውም የመከላከያ ወጪ ሚስጢር
ነው የሚል ነበር፡፡
ይህንን ተከትሎ የፓርላማ አፈጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ በቴሌቪዥን ቀርበው “ባልተሟላ ሰነድ
ወጪ ተደረገ ማለት ብሩ ተበላ ማለት አይደለም” በማለት ማብራሪያ ለመስጠትና ተቋሙን ከተጠያቂነት ነጻ ለማድረግ
ሞክረዋል፡፡
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከተሾሙ በኋላ የመጀመሪያቸው የሆነውን መግለጫ ትላንት ጠዋት
በጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጡበት ወቅት በተመሳሳይ መንገድ መከላከያን ኦዲት ማድረግ
ሚስጢር ማባከን መሆኑን በመግለጽ በቀጣይ ሁኔታውን ለማስተካከል አዲስ ሕግ እንደሚወጣ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡
ዋና ኦዲተር በአዋጅ ቁጥር 669/2002 መሰረት የፌዴራል የመንግስት ተቋማትን ኦዲት የማድረግና የማስደረግ ሙሉ ሥልጣን
እንደተሰጠው ጠቅላይ ሚኒሰትሩ አስታውሰው በዚህ ሕግ መሰረት ባለፉት ዓመታትም መከላከያን ጨምሮ ሁሉንም ተቋማት ኦዲት ሲያደርግ መቆየቱን አስረድተዋል፡፡
አቶ መለስ ዜናዊ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ በሚያዚያ ወር 2004 ዓ.ም የ2003 የሂሳብ ሪፖርት ለፓርላማው ቀርቦ እንደነበር በዚህም ሪፖርት መሰረት
ከተወቀሱት ተቋማት መካከል መከላከያ አንዱ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ በ2003 በጀት ዓመት በመከላከያ 133 ነጥብ
8 ሚሊየን ብር ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ መኖሩን፣ የተሟላ ማስረጃ ሳይቀርብ 19 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በወጪ
ተመዝግቦ መገኘቱን ሪፖርት አድርጓል፡፡  በተጨማሪም የወጪውን ትክክለኛነት ማረጋገጥ ካልተቻለው ገንዘብ መካከል 1
ነጥብ 9 ቢሊየን ብር የመከላከያ ሲሆን ፣ 54 ነጥብ 3 ሚሊየን ደግሞ ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ 33
ነጥብ 34 ሚሊየን ብር የአገር ውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ መሆኑ መጠቀሱ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ መ/ቤቱ
እንደዘንድሮ ከፍተኛ ቅሬታ ያላቀረበ ሲሆን የዘንድሮ ቅሬታ ምናልባትም በአዲሱ ጠ/ሚኒስትር ላይ ተጽዕኖ በማሳደር
ነገሩን ለመሸፋፈን የታሰበ ሳይሆን እንደማይቀር ተገምቷል፡፡
ምንጮቻችን እንደገለጹት በአገሪቱ ከፍተኛ ሙስና ከሚፈጸምባቸው ተቋማት መካከል ግንባር ቀደሙ መከላከያ መሆኑን
አስታውሰው አንድ ወርሃዊ ደመወዙ 4 ሺ ብር የማይሞላ ከፍተኛ የመከላከያ ሹም በአዲስአበባ ቁልፍ ቦታዎች ጭምር
በሚሊየን ብር የሚገመቱ ቪላዎችንና ሕንጻዎችን የሚገነባበት እንዲሁም ትልልቅ ንግዶችን የሚያንቀሳቅስበት ሁኔታ
የአደባባይ ሚስጢር ነው በማለት የእነአቶ ኃይለማርያም ሙግት ጥቅሙ ለሙሰኞቹ ነው ብለዋል፡፡
አዲሱ ሕግ በቀጣይ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ዋና ኦዲተር ሕጉ እስኪጸድቅ
መከላከያና የደህንነት ተቋማትን ኦዲት እንዳያደርግ መታዘዙንም ምንጮቻችን አረጋግጠዋል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ 60 ከፍተኛ ጀኔራሎች መካከል 58ቱ በትጥቅ ትግሉ ወቅት የህወሀት አባል ሆነው የመጡ ናቸው።
መከላከያን ከላይ ሆነው የሚዘወሩት 7ቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በሙሉ የህወሀት ታጋዮች ናቸው። ባለፉት 22 አመታት በዚህ ከፍተኛ
አመራር ውስጥ የሌላ ብሄር ተወላጅ ተካቶ አያውቅም።
በሌላ በኩል ደግሞ አቶ ሀይለማርያም በአባይ ግድብ ዙሪያ ከተቃዋሚዎች ጋር እንደማይነጋገሩ አስታውቀዋል።
ኢሳት ዜና

ጄ/ል ክንፈ ተመለሱ፤ መከላከያ ውጥረት ነግሷል – (ከኢየሩሳሌም አርአያ)


የብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ብ/ጄነራል ክንፈ ዳኘው ላለፉት ሶስት ወራት ገደማ ከስልጣናቸው ታግደው ከቆዩ በኋላ በዚህ ሳምንት ወደ ሃላፊነት መመለሳቸውን የቅርብ ምንጮች ገለፁ። በጄ/ል ሳሞራ የኑስ ትእዛዝ ታግደው ከቆዩት ከፍተኛ ጄነራሎች መካከል አንዱ ጄ/ል ክንፈ እንደሚገኙበት የጠቆሙት ምንጮቹ ስልካቸውን በመጥለፍ በእንቅስቃሴያቸው ዙሪያ ክትትል ይደረግባቸው እንደነበር አስታውቀዋል። ጄ/ል ክንፈ በሳሞራ ታግደው የቆዩት የነአዜብ/በረከትን ቡድን በመቃወም ከነስብሃት ቡድን ጋር በመሰለፋቸው እንደሆነ ምንጮቹ አመልክተዋል። የጠ/ሚ/ር መለስን ሕልፈት ተከትሎ በመከላከያ ከፍተኛ ጄነራሎች መካከል የተፈጠረው ያለመግባባት ስር እየሰደደ መሄዱንና የልዩነቱ መንስኤም በሕወሐት የተፈጠረው ቀውስ – ጄነራሎቹ ጎራ እንዲለዩ ጫና ማሳደሩን ያመለከቱት ምንጮች፣ አክለውም ልዩነቱ በአገር ጉዳይ ዙሪያ ሳይሆን አንዱ ሌላኛውን በማስወገድ የራስን ጥቅም አስጠብቆ በስልጣን ለመቆየት የሚደረግ የሙስና መጠላለፍ ነው ብለዋል። ጄ/ል ክንፈ የብረታ ብረት ኮርፖሬሽን ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙት በሟቹ ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ እንደሆነ ያስታወሱት ምንጮቹ ከስልጣን ሊያግዳቸውም ሆነ ሊያወርዳቸው የሚችለው በህግ ስልጣን የተሰጠው ጠ/ሚኒስትሩ መሆኑን ያስረዳሉ። በዚሁ መሰረት ስልጣኑ በአዋጅ የተቀመጠው ለጠ/ሚ/ር ሃ/ማሪይም ቢሆንም – በግልፅ የሚታየው ግን ከህግ ውጭ የጄ/ል ሳሞራ ፈላጭ ቆራጭ ውሳኔ ከመሆኑ በተጨማሪ የታገደውን ጄ/ል ወደ ቦታው የሚመልሰው በተቃራኒው የቆመውና በሕወሐት ውስጥ ያለው የነስብሃት ቡድን መሆኑን ምንጮቹ ያመለክታሉ። አቶ መለስ ይዘውት የቆዩትና “በሕገ-መንግስቱ ተሰጠ” ከተባለው ስልጣን በአብዛኛው ለጠ/ሚ/ር ሃ/ማሪያም ሊሰጥና ሊተላለፍ አልቻለም ሲሉ የጠቆሙት ምንጮቹ ቁልፍ የሆነው የጦር ሃይሎች ጠ/አዛዥነትን ጨምሮ በርካታዎቹ ሕገ-ወጥ በሆነ ሁኔታ በሕወሐት ሰዎች ቁጥጥር ስር መውደቃቸውን አመልክተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ- ጄ/ል ሳሞራ የሚመሩት ስብሰባ በመከላከያ ከፍተኛ ጄነራሎች ተሳታፊነት በዚህ ሳምንት ሲካሄድ መሰንበቱን ምንጮች ጠቆሙ። ውጥረትና ያለመረጋጋት በተስተዋለበት የሳሞራ ንግግር በዋና አጀንዳነት የቀረበው የግንቦት ሰባት ጉዳይ ሲሆን በዚህም ፥ « ግንቦት ሰባት በመንግስትና በሕገ-መንግስቱ ዙሪያ መጠነሰፊ አደጋ ጋርጦብናል፤ በግንቦት ሰባት የሚደገፉ በአገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች ላይ አፋጣኝ እርምጃ ልንወስድ ይገባል፤» ማለታቸውን የገለፁት ምንጮቹ፣ ሳሞራ «ለምሳሌ.» ሲሉ ሰማያዊ ፓርቲን እንዲሁም « አንዳንድ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች» በማለት መፈረጃቸውን አስታውቀዋል። በተጨማሪ የሙስሊሙ ማህበረሰብ እያነሳ ያለውን ፍትሃዊ የመብት ጥያቄ፣ ሳሞራ ከግንቦት ሰባት ጋር ለማያያዝ መሞከራቸውን ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል። በሌላም በኩል የኢንፎርሜሽንና መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና ሃላፊ ብ/ጄነራል ተክለብርሃን ወ/አረጋይ በበኩላቸው፥ ከእንግሊዝ አገር ረቀቅ ያለ መሳሪያ በማስመጣት በስካይፕ ተቃዋሚዎች የሚያደርጉትን ግንኙነቶች በመጥለፍና ተዛማች የስለላ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ከገለፁ በኋላ « ግንቦት ሰባት ከግብፅ ጋር ግንኙነት እንዳለው ለህዝቡ ከነገርነው ከጎናችን ይቆማል፣ ግንቦት ሰባትን በማውገዝ የእንቅስቃሴው ተባባሪ አይሆንም፣ በአገር ውስጥ ያሉትም ተቃዋሚዎች ላይ የሚወሰደውን እርምጃ ህዝቡ አይቃወምም፤ እንዳውም ለመንግስት ድጋፍ ይሰጣል፤» በማለት በተሰብሳቢ መኮንኖች ጭምር ገረሜታን የፈጠረ ንግግር ማድረጋቸውን ምንጮቹ አስታውቀዋል። በዚህም ለሕዝብ ያላቸውን ግምትና የግንዛቤ ደረጃ ያመላከተ ነው ያሉት ምንጮቹ የጄ/ል ተክለብርሃን የእውቀት ደረጃ ምን ድረስ እንደሆነ ያሳየ ነው ብለዋል። የኤንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ በአቶ ደብረፂዮን ጭምር በበላይነት እንደሚመራና አቶ ሃ/ማሪያም የሚያውቁት እንደሌለ ምንጮቹ አያይዘው ጠቁመዋል። በሕገ – መንግስቱ መከላከያ ከየትኛውም ፖለቲካ ፓርቲ ገለልተኛ እንደሆነ ቢደነግግም፣ ከወረቀት በዘለለ ተግባር ላይ ሲውል እንደማይታይና የነሳሞራና ተከታዮቻቸው ተደጋጋሚ አቋምና ተግባር በቂ ማስረጃና ማሳያ መሆኑን ምንጮቹ በሰጡት አስተያየት አስረድተዋል። በመጨረሻም፥ የታገዱ ሌሎች ጄኔራሎችን ጉዳይ እንዲሁም ባለፈው ወር በሳሞራ ትእዛዝ የተባረሩ የሕወሐት ጄነራሎች ወደ ከፍተኛ ንግድ መሰማራት በተመለከተ ዝርዝር መረጃውን ይዘን እንመለሳለን።

Saturday, June 29, 2013

የአብዬን ወደ እምዬ

ወያኔና ከወያኔ አፍ የሰሙትን ሁሉ እንደበቀቀን እየደጋገሙ የሚያነበንቡ ሎሌዎች የራሳቸውን መልክ የሚያዩበት መስታወት የተቸገሩ ይመስላል። ወየኔና ሎሌዎቹ እራሳቸውን ማየት ስለተሳናቸው ህዝብም ልክ እንደ እነሱ ኣራሱን የማያይና እነሱንና እኩይ ስራቸዉን የማያዉቅ እየመሰላቸው ሄዷል፡፡ ለዚህም ነዉ በግፈኛ አገዛዛቸው ተንገፍግፎ የሚቃወማቸውን ሁሉ ጥላሸት ለመቀባትና በራሳቸው ስም ለመጥራት ሲንጠራሩ የሚታዩት።

የወያኔ ዘረኞች የኢትዮጵያን ተቃዋሚ ኃይሎች በሙሉ በፀረ-ኢትዮጵያዊነትና የአገርን ጥቅም ለባዕድ አሳልፎ በመሸጥ ሲከስሱ ስንሰማ አይናቸዉንና ፊታቸዉን ታጥበዉ አይነ ደረቅ ለመመሰል ስንት ኪሎ ጨው እንደፈጀባቸዉ መገመት ያዳግታል።

በአገራችን ታሪክ ውስጥ እንደወያኔ በኢትዮጵያ ህልውናና በወሳኝና ዘላቂ ጥቅሞቿ ላይ የዘመተ ኃይል ኖሮም ተፈጥሮም አያውቅም። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጀግኖች አባቶቻችን አጽም ያረፈበትን መሬት በስጦታ ለጎረቤት አገር እናካችሁ ብሎ የሰጠ ማነዉ? ማነው በሽፍትነት ዘመኑ ለተደረገለት ውለታና ተቀናቃኞቹን እንዲጠብቁለት በማሰብ የኢትዮጵያን ድንበር እንደ ዳቦ እየገመሰ ለባዕዳን የሸጠው?

ማነው የገዛ ወገኑን ከአያት ቅድመ አያት አጽመ ርስቱ ላይ እያፈናቀለ አንድ ሲኒ ቡና በማይገዛ ገንዛብ ለምለም መሬታችንን ለባእዳን የሚያቀራምተው? ማነው በህዝብ ስም በልመናና በችሮታ የተገኘን ገንዘብ እየዘረፈ ከአገርና ከህዝብ ደብቆ የባእድ አገር ባንኮችን የሚያደልበው? ኢትዮጵያ በሶማሊያ በተወረረችበት በ1970ዎቹ አመታት የሞቃዲሾን ፓስፖርት ተሸክመው ይንጎማለሉ የነበሩት የዛሬዎቹ የወያኔ አለቆች መሆናቸውን የኢትዮጵያ ህዝብ ገና አልረሳዉምኮ!

የዛሬዎቹ የወያኔ መሪዎች ትናንት የኢትዮጵያን ሰላምና አንድነት ማየት ከማይፈልጉ የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች ጋር እጅና ጓንት ሆነዉ የኛን የጎሳ ድርጅት እስከረዳችሁ ድረስ ኢትዮጵያን እናደክምላችኋለን የሚሉ ጸረ አገርና ጸረ ህዝቦች ነበሩ።እነዚህ የለየላቸዉ ከሀዲዎች ዛሬ አይናቸዉን በጨው አጥበዉ እራሳቸዉን የኢትዮጵያ ጥቅም አስከባሪ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነትና ለአገር አንድነት መከበር የሚታገሉትን ዉድ የኢትዮጵያ ልጆች የአገር ጠላት ብሎ ለመጥራት የሚያበቃ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያክል የሞራል ብቃት የላቸውም።

ወያኔዎች ስልጣን በያዙ ማግስት በጻፉትና እነሱን ሲጠቅም በሚጠቅሱት አገርንና ህዝብን ሲጠቅም ግን እየዳጡ በሚያልፉት ህገመንግስት ዉስጥ ደደቢት በረሃ የወሰዳቸዉን ዋነኛ አላማ መገነጣጠልን እንደ አገር ጥቅም በጹሁፍ ካልሰፈረ ብለው ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ የነበሩበትን ጊዜ እኛ የኢትዮጵያ ነገር የሚቆረቁረን ወገኖች አልረሳነውም። ለመሆኑ ሌሎችን በጸረ-ኢትዮጵያዊነት የሚከሰው ወያኔ እውነት ኢትዮጵያን ከወደደ መገነጣጠልን ለምን ተመኘላት? መገነጣጠልን የመሰለ አደጋ እንደ ብሔራዊ የአገር ጥቅም አይቶ የራሱን ምኞት በህግመንግስት ደረጃ ያጸደቀዉ ወያኔ እንዴት ሆኖ ነው ለኢትዮጵያ አንድነትና ክብር የሚጋደሉና የሚታገሉ ልጆቿን በሀገር ጠላትነት የሚከስሰው? የኢትዮጵያ ህዝብ ከወያኔ ጋር የሚደረገዉን ትግል ከመብትና ከነጻነት ትግል ባሻገር እንደ አገር አድን ትግል አድርጎ የሚመለከተዉ ይህንኑ ወያኔ በአገራችን ብሄራዊ ጥቅሞች ላይ በተደጋጋሚ ያሳየዉን ጠላትነት በመገንዘብ ነዉ።

የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔ ተቃዋሚ ኃይሎችን በጅምላ የአገር ጠላት ለማስመሰል በሚቆጣጠራቸዉ የመገናኛ አዉታሮችና በታማኝ ሎሌዎቹ በኩል የጀመረዉን የስም ማጥፋት ዘመቻ ከወዲሁ ተረድቶ “የአብዬን ወደ እምዬ” ብሎ ትግሉን ከቀጠለ ዉሎ አድሯል። ወያኔና ለሆዳቸው ያደሩ ሎሌዎች ሁለመናቸውን የወረሰውን የፀረ-ህዝብና ጸረ ኢትዮጵያዊነት እከክ ማንም ላይ ማራገፍ አይችሉም። ድፍን ኢትዮጵያ ማንነታቸውን አሳምሮ ያውቃልና።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

! .... ትንሽ ስለ ጀዋር መሓመድ ......!



አንድ ጓደኛየ አንድ የተቀናበረ ቪድዮ በፌስቡክ ገፄን ለጠፈልኝ፤ እንዳነበው እየጋበዘኝ መሆኑ ነው። ቪድዮው ስለ ጀዋር ነው። ግን የሌሎች ሰዎች ስሞችም (የኔን ጨምሮ) ተጠቅሷል። ልጁ ቪድዮውን ሲጋብዘኝ አንዳንድ ዲያስፖራ ተቃዋሚዎች ስለኔ ያላቸው አመለካከት እንዳውቅና ኢህአዴግ መቃወሜን እንዳቆም 'በአሪፍ' ተፅዕኖ ማሳደሩ ነው፤ ይህን ድምዳሜ የመጣልኝ ልጁ (ቪድዮው የላከልኝ) ከዚህ በፊት ይልክልኝ በነበሩ ተመሳሳይ መልእክቶች በመነሳት ነው። ይህን የፖለቲካ ስትራተጂ እንደማይሰራ በተደጋጋሚ ለማረጋገጥ ሞክርያለሁ።

ግን ...

ሰዎች በኔ ሓሳብ ሊደሰቱ ወይ ሊናደዱ ይችላሉ፤ መደሰትም መናደድም መብታቸው ነው። እኔ ደግሞ የፈለኩትን የመፃፍ መብት አለኝ። ስለዚህ የኔ አቋም ሌሎች ሰዎች በሚሰጡኝ ምላሽ የተንጠለጠለ አይደለም።

ወደ ጀዋርና ቪድዮው ልመለስ። ቪድዮው ጀዋርና ሌሎች ሰዎች ስለተናገሩት ሓሳብ ቀነጫጭቦ ያቀርባል። በመጀመርያ ቪድዮው ትኩረት አልሰጠሁትም ነበር። በኋላ ስለ ቪድዮው የተፃፉ ነገሮች ሳነብ ግን ትኩረት እንደሚያስፈገው ገባኝ።

ባጠቃላይ ሲታይ የተቀናበረውን ቪድዮ አልወደድኩትም። አንደኛ የተቀመጠው የጀዋር ሓሳብ የተቆራረጠ ነው። ለድምዳሜው የሰጣቸው ማስረጃዎች በትክክል በቪድዮው አልተካተቱም። አንድ ጥሩ የነበረ ሓሳብ ቆራርጠን በማቅረብ ጥላሸት መቀባት ይቻላል። ስለዚህ ጠቅላላው የቀረበ አመክንዮ በተፈለገው መጠን ስላልቀረበ በቪድዮን በቀረቡ የተቀነጫጨቡ ሓሳቦች መገምገም አንችልም።

ሁለተኛ በቪድዮው የቀረበው የተቀነባበረ ሓሳብ ጀዋርን ለመገምገም ያስችለናል ብለን ከተነሳን የተናገረው ነገር የልጁን ስም ለማጥፋት በቂ ምክንያት ይሆናል ወይ? የሰጠው ሓሳብ የራሱ (የግሉ) አስተያየት ነው። 'ኦሮሞዎች በደል ይደርሳቸው ነበር' ብሎ ማለት 'ኢትዮዽያን መጥላቱ' ያሳያል ወይ? የብሄር ጭቆና መኖሩ ሓሳብ መሰንዘር 'ኢትዮዽያዊ ስሜት' እንደሌለው ምክንያት ወይ ማረጋገጫ ሊሆን ይችላል ወይ?

ስለ ኢትዮዽያ ስናወራ ስለኢትዮዽያውያን እየተናገርን ነን። ኢትዮዽያውያን ህዝቦች ናቸው። ህዝቦቹም ኦሮሞዎች፣ አማራዎች፣ ትግራዮች፣ ጉራጌዎች፣ ሶማሊዎች፣ ደቡቦች፣ ጋምቤላዎች፣ ቤኑሻንጉሎች ... ወዘተ ናቸው። 'ጉራጌ ተበደለ' ሲባል ኢትዮዽያዊ እየተበደለ ነው ማለት ነው። ስለዚህ ጀዋር 'ኦሮሞች ተበድለዋል' በማለቱ የተፈጠረ ችግር ምንድነው??? እንኳንም በድሮ ዘመን አሁንም እኮ 'ጭቆና አለ' ብለን እየተከራከርን ነን።

ሦስተኛ ጀዋር የሰጠው አስተያየት ጥሩ አይደለም ብለን እንነሳ፤ ታድያ ማድረግ ያለብን ጉዳይ ስም ለማጥፋት መሯሯጥ ሳይሆን አስተያየቱ ስህተት መሆኑ በሓሳብ ማሳመን መቻል ነው። በሰጠው አስተያየት ላይ የሓሳብ ክርክር መክፈት ይቻላል። አስተያየቱ 'ስህተት' ስለመሆኑ ማረጋገጥ የምንችል ከሆነ ጀዋርን ለማስተካከል እንዴት ያቅተናል?

አራተኛ አንድ ሰው የተለየ አስተያየት ስለሰጠ 'የኢትዮዽያ ጠላት' አድርጎ መፈረጅ መፍትሔ ይሆናል ወይ? ሁሉም ሰው ስለ አንድ ጉዳይ ተመሳሳይ አቋም ይኖረው ዘንድ ግድ አይደለም። የምንታገለው አንድ ዓይነት አስተሳሰብ እንዲኖረን ለማድረግ ሳይሆን እንደየምርጫችን በነፃነት መኖር እንድንችል ነው።

በመጨረሻም

ጀዋር በያዘው አቋም ልዩነት ቢኖረኝም በሰጠው አስተያየት ግን አልተከፋሁም፤ ጥፋቱም አልገባኝም። የብሄር ጭቆና እንደነበር (አሁንም ችግሩ በተገቢ መንገድ እንዳልተፈታ) ከጀዋር ጋር እስማማለሁ። በአሁኑ ሰዓት (ችግሩ ለመፍታት) ምን መደረግ አለበት በሚለው (ብሄርን ከሀገር ማስቀደሙ) ግን ከጀዋር ጋር የሓሳብ ልዩነት አለኝ።

እንደኔ ከሆነ የዘመናት የፖለቲካ ችግሮቻችን መፍታት የምንችለው ታሪክን እያስታወስንና ብሄርን እያስቀደምን የሀገራችን አንድነት በሚያዳክም መልኩ በመወያየት ሳይሆን የነበረው ጭቆና እንዲወገድ አብረን በመታገልና በእኩልነትና በአንድነት የምንኖርባት ኢትዮዽያ እውን በማድረግ ይመስለኛል።

ጀዋር መሓመድ በጣም ከማደንቃቸው ብርቅዬ ወጣት ኢትዮዽያውያን የፖለቲካ ተንታኞች አንዱ ነው። ጀዋር አድናቆቴን ይድረሰህ።

በሓሳብ መለያየት ጥፋት አይደለም። ስለዚህ የሰው ስም ለማጥፋት ዘመቻ መክፈት ተገቢ አይደለም።

ኢትዮዽያችንን ይባርክልን፤ አሜን።

It is so!!!

በአብርሃ ደስታ

ተመስገን ደሳለኝ ለማን ደስ ይበለው ብሎ ጠፋ!?


ባለፈው ጊዜ አንድ ወዳጄ ጋር አዲሳባ ስልክ ደውዬ ሳናግረው በአካባቢው ከእርሱ ድምጽ ጎልቶ የሚሰማ የመኪና ጥሩንባ ሰማሁና ይሄ ሁሉ የመኪና ጥሩምባ ምንድነው… ብዬ ጠየኩት፡፡

ሃይለማሪያም ደሳለኝ እየገቡ ወይም እየወጡ ነው መሰለኝ መንገድ ተዘጋግቷል፡፡ አለኝ፡፡

ወዲያውም ቀጠል አድርጎ፤ እንደ ሀቁ ቢሆን ኖሮ መንገድ መዘጋጋት የነበረበት ለሀይለማሪያም ደሳለኝ ሳይሆን ለተመስገን ደሳለኝ ነበር… አለኝና በቁጭት፤ ይሄው የሚያጅቡትን አያቀውቁምና… እልኩ እያታዘብኩ ነው…! ሲል አወጋኝ!

ተመስገን ደሳለኝ ገዢውም ተገዢውም ፓርቲ ሊያመሰግነው የሚገባ ጋዜጠኛ ነው፡፡ ነገር ግን ገዢዎቻችን ማመስገን የሚቆጥር ይመስል ሰውን ማመስገን አይወዱም፡፡ ስለዚህ ተሜንም በማመስገን ፈንታ ከሰሱት፡፡ ጎሽ በማለት ፈንታ እንደ ጎሽ ሊወጉት ቀንዳቸውን አሾሉበት፡፡ እሰይ በማለት ምትክ ሰይ ባንከረባብት ብለው ለሁለቱም አሰቡት፡፡ (ለማሰርም ለማሰደድም) (ሰይ ባንከረባብት በልጅነታችን ብይ ጨዋታ ላይ ተወርዋሪዋ ብይ ጉድጓዳ ውስጥ ብትገባም የተቃራኒውን ብይ ብትመታም ነጥቡ እንዲያዝልን ውል የምንገባባት ቃል ነበረች፡፡)

ተመስገን ደሳለኝ እንዲሰደድ መንግስት ከፀሎት ጀምሮ ሁሉንም አይነት የትግል ስልቶችን እንደተጠቀመበት ትዝ ይለኛል፡፡ ለምሳሌ ባለፈው ጊዜ ምንም የቀጠሮ ወረቀት ወይም መጥሪያ ሳይሰጠው በራዲዮን፤ “ተመስገን ደሳለኝ በሌለበት የፍርድ ሂደቱ ታየ ለሚቀጥለው ጊዜ ፖሊስ ይዞ እንዲያቀርበው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል!” የሚል አይነት ዜና በሰላም ቁጭ ብሎ ሻይ በሚጠጣበት ካፌ ውስጥ ሰማ፤ (እናጋን ካልን ደግሞ ዜናውን እንደውም ያነበቡት ተሜ ልክ ዜና ሲሰማ አይተው ነው…! ማለት እንችላለን…) የዚህ ዜና አላማ ግልፅ ነበር፡፡ ተሜ ደንግጦ ፖሊስ ሳይዘው በፊት መንገዱን እንዲያያዘው ማድረግ ነበር፡፡ ወዳጃችን ግን፤ ብታስሩኝ ባለ ጊዜም ባለ ብረትም ናችሁና እግሬ እምቢ ማለት አይቻለውም፡፡ ለመሰደድ ግን እሺ የሚል እግር የለኝም፡፡ ብሎ እንቅጩን ነገራቸው እና የመጣው ምጣ ብሎ ቁጭ አለ…

በነገራችን ላይ ተመስገን እስከ አሁን ድረስ በመንግስት የተሰነዘረበት ክስ ስፍር ቁጥር የለውም፡፡ እንደው የሪከርድ መዝጋቢ መስሪያ ቤቶች የሚያስታውሳቸው አጥተው እንጂ ከዚህ ሁሉ ክስ ጋር አብሮ መኖር የቻለ ጋዜጠኛ ብለው ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ የሚያሰፍሩት ሁሉ ይመስለኛል፡፡ መንግስታችን በክስ ላይ ክስ ሲደራርብ ሲደራርብ ክሱ ተቆልሎ አለመናዱም የእግዜር ተዓምር ነው፡፡ አንዱ ሳይቋጭ አንዱን አንዱ ሳይቋጭ አንዱ ክስ ሲመጣ በአሁኑ ሰዓት ተመስገን ደሳለኝ ከሃምሳ በላይ ክሶች ጋር ተመስገን ብሎ እየኖረ ነው፡፡

የተሜ እና የእኛ ፍትህ ጋዜጣ “መለስ ሞቱ” በማለቷ እኛ ሳንል ምን ሲደረግ እንዲህ ትያለሽ ተብላ ከሳላሳ ሺህ ኮፒ በላይ እንድትቃጠል ተደረገች፡፡ (የመለስ አምልኮ ይሎዎታል ተመስገን…!) አንዱ ሲዘጋ በአንዱ እንከሰታለን በምትለው ስትራቴጂ መሰረት፤ አዲስ ታይምስ ተተካች፡፡ አዲስ ታይምስ ደግሞ “ብር ከየት አምጥታችሁ ነው…” ተብላ ህትመቷ ተከለከለ፡፡ መንግስታችን እንደሆነ ኮሚክ ነው ጮክ ብለን በያይነቱ ስናዝ ራሱ “ብር ከየት አምጥተው ነው” ብሎ ይጨንቀዋል፡፡ በእርሱ ቤት እርሱ አበል ያልሰጠው ሰው፤ ወይም ከአዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም ያልተበደረ ሰው ምንም ገንዘብ የለውም…!

ተመስገን እና ጓደኞቹ እጅ መስጠት ብሎ ነገር አያውቁም ነበር፤ እና ከየትም ከየትም ብለው ድጋሚ ልዕልና ጋዜጣን አበረከቱልን፡፡ መንግስት መንግስት ሆኖ እንጂ… በብስጭት ካቲካላ ይጠጣ ነበር፡፡ ግን ሳይጠጣም ሞቅ አለው፡፡ ሰከረም፡፡ እናም ልዕልናንም ጥርቅም አድርጎ ዘጋት፡፡ (ይህ ውሳኔ የሞቅታ ካልሆነ ሌላ ሊሆን አይችልም)

ተመስገን ደሳለኝ ሲናገር ሰዎቻችን ደስ አይላቸውም፡፡ እናም በተቻለ አቅም ዝም ማሰኘት ይፈልጋሉ፡፡ ልጁ ግን በቀላሉ ዝም ብሎ የሚያስደስታቸው አልነበረም፤ በማህበራዊ ድረገፆች የሚተነፍሰውን ይተነፍስ ጀመር፡፡

ኢህአዴግ ሰው እንደማትንቅ ያወኩት እኔ ምስኪኑን ሳይቀር ለመከታተል የደህንነት ሰው የመደበች ዕለት ነው፡፡ ለተመስገን ደሳለኝማ ሁሉን አቀፍ የትግል ስልት ነው የተጠቀመችበት፡፡ በእውነቱ ከሆነ፤ ለአንድ ግለሰብ ሁሉን አቀፍ የትግል ስልት መጠቀም ትልቅ የሀይል ብክነት ነው፡፡ ፍጹም ተመጣጣኝ ያልሆነ ርምጃ፤ ጎጆ ቤትን በሚሳኤል እንደ መደብደብ በሉት…

ተሜ በኢህአዴግ ክሶች ብዛት፤ በኢህአዴግ ሚዲያዎች ማስፈራራት፣ በኢህአዴግ የደህንነት ሰዎች ከበባ፣ በኢህአዴግ ማተሚያ ቤቶች አድማ አበሳውን አየ፡፡

“አንበሳው” መንግስታችን ተመስገን ግለሰብ ነው ብሎ አልናቀውም፡፡ ያለውን አቅም ሁሉ ተጠቅሞ ሊገድበው ተንቀሳቅሷል፡፡ እርሱን ለመገደብ ያላደረገው ነገር ቢኖር ቦንድ ግዙ ብቻ አላለንም፡፡ ለአባይ የምንገዛው ቦንድ ብዙ ነገር ይገድባልና!

አሁን ተመስገን ደሳለኝ ከሜዳው ላይ ጠፍቷል፡፡ ከመንግስታችን ሃይል የተሞላበት አጨዋወት አንጻር እስከዛሬም በቃሬዛ አለመውጣቱ የሚገርም ነበር፡፡ ነገር ግን ያንን ሁሉ ችሎ ሜዳው ላይ ስናየው እኛ ደስ ይለን ነበር፡፡ አሁን ታድያ ሲጠፋብን ጊዜ በአዲስ መስመር ላይ ጮክ ብለን እንጮሃለን እንጂ እንደምን ዝም እንላለን…

ተመስገን ደሳለኝ ሆይ ማን ደስ ይበለው ብለህ ጠፋህ…!

Amnesty International 2013 Report: Ethiopia


Amnesty International 2013 Report: Ethiopia

Source: Amnesty International 2013 Report: Ethiopia Background Freedom of expression Human rights defenders Torture and other ill-treatment Arbitrary arrests and detentions Excessive use of force Conflict in the Somali region Forced evictions The state stifled freedom…
  • Background
  • Freedom of expression
  • Human rights defenders Torture and other ill-treatment
  • Arbitrary arrests and detentions
  • Excessive use of force
  • Conflict in the Somali region
  • Forced evictions
The state stifled freedom of expression, severely restricting the activities of the independent media, political opposition parties and human rights organizations. Dissent was not tolerated in any sphere. The authorities imprisoned actual and perceived opponents of the government. Peaceful protests were suppressed. Arbitrary arrests and detention were common, and torture and other ill-treatment in detention centres were rife. Forced evictions were reported on a vast scale around the country.
Background
In August, the authorities announced the death of Prime Minister Zenawi, who had ruled Ethiopia for 21 years. Hailemariam Desalegn was appointed as his successor, and three deputy prime ministers were appointed to include representation of all ethnic-based parties in the ruling coalition.Amnesty International 2013 Report: Ethiopia
The government continued to offer large tracts of land for lease to foreign investors. Often this coincided with the “villagization” programme of resettling hundreds of thousands of people. Both actions were frequently accompanied by numerous allegations of large-scale forced evictions.
Skirmishes continued to take place between the Ethiopian army and armed rebel groups in several parts of the country – including the Somali, Oromia and Afar regions.
Ethiopian forces continued to conduct military operations in Somalia. There were reports of extrajudicial executions, arbitrary detention, and torture and other ill-treatment carried out by Ethiopian troops and militias allied to the Somali government.
In March, Ethiopian forces made two incursions into Eritrea, later reporting that they had attacked camps where they claimed Ethiopian rebel groups trained (see Eritrea entry). Ethiopia blamed Eritrea for backing a rebel group that attacked European tourists in the Afar region in January.
Freedom of expression
A number of journalists and political opposition members were sentenced to lengthy prison terms on terrorism charges for calling for reform, criticizing the government, or for links with peaceful protest movements. Much of the evidence used against these individuals consisted of examples of them exercising their rights to freedom of expression and association.
The trials were marred by serious irregularities, including a failure to investigate allegations of torture; denial of, or restrictions on, access to legal counsel; and use of confessions extracted under coercion as admissible evidence.
  • In January, journalists Reyot Alemu, Woubshet Taye and Elias Kifle, opposition party leader Zerihun Gebre-Egziabher, and former opposition supporter Hirut Kifle, were convicted of terrorism offences.
  • In June, journalist Eskinder Nega, opposition leader Andualem Arage, and other dissidents, were given prison sentences ranging from eight years to life in prison on terrorism charges.
  • In December, opposition leaders Bekele Gerba and Olbana Lelisa were sentenced to eight and 13 years’ imprisonment respectively, for “provocation of crimes against the state”.
Between July and November, hundreds of Muslims were arrested during a series of protests against alleged government restrictions on freedom of religion, across the country. While many of those arrested were subsequently released, large numbers remained in detention at the end of the year, including key figures of the protest movement. The government made significant efforts to quash the movement and stifle reporting on the protests.
  • In October, 29 leading figures of the protest movement, including members of a committee appointed by the community to represent their grievances to the government, and at least one journalist, were charged under the Anti-Terrorism Proclamation.
  • In both May and October, Voice of America correspondents were temporarily detained and interrogated over interviews they had conducted with protesters.
The few remaining vestiges of the independent media were subjected to even further restrictions.
  • In April, Temesgen Desalegn, the editor of Feteh, one of the last remaining independent publications, was fined for contempt of court for “biased coverage” of the trial of Eskinder Nega and others. Feteh had published statements from some of the defendants. In August, he was charged with criminal offences for articles he had written or published that were deemed critical of the government, or that called for peaceful protests against government repression. He was released after a few days’ detention and the charges were dropped.
In May, the authorities issued a directive requiring printing houses to remove any content which could be defined as “illegal” by the government from any publications they printed. The unduly broad provisions of the Anti-Terrorism Proclamation meant that much legitimate content could be deemed illegal.
  • In July, an edition of Feteh was impounded after state authorities objected to one cover story on the Muslim protests and another speculating about the Prime Minister’s health. Subsequently, state-run printer Berhanena Selam refused to print Feteh or Finote Netsanet, the publication of the largest opposition party, Unity for Democracy and Justice. In November, the party announced that the government had imposed a total ban on Finote Netsanet.
A large number of news, politics and human rights websites were blocked.
In July, Parliament passed the Telecom Fraud Offences Proclamation, which obstructs the provision and use of various internet and telecommunications technologies.
Human rights defenders
The Charities and Societies Proclamation, along with related directives, continued to significantly restrict the work of human rights defenders, particularly by denying them access to essential funding.
  • In October, the Supreme Court upheld a decision to freeze around US$1 million in assets of the country’s two leading human rights organizations: the Human Rights Council and the Ethiopian Women Lawyers Association. The accounts had been frozen in 2009 after the law was passed.
  • In August, the Human Rights Council, the country’s oldest human rights NGO, was denied permission for proposed national fundraising activities by the government’s Charities and Societies Agency.
It was reported that the Agency began enforcing a provision in the law requiring NGO work to be overseen by a relevant government body, severely compromising the independence of NGOs.
Torture and other ill-treatment
Torture and other ill-treatment of prisoners were widespread, particularly during interrogation in pre-trial police detention. Typically, prisoners might be punched, slapped, beaten with sticks and other objects, handcuffed and suspended from the wall or ceiling, denied sleep and left in solitary confinement for long periods. Electrocution, mock-drowning and hanging weights from genitalia were reported in some cases. Many prisoners were forced to sign confessions. Prisoners were used to mete out physical punishment against other prisoners.
Allegations of torture made by detainees, including in court, were not investigated.
Prison conditions were harsh. Food and water were scarce and sanitation was very poor. Medical treatment was inadequate, and was sometimes withheld from prisoners. Deaths in detention were reported.
  • In February, jailed opposition leader, Andualem Arage, was severely beaten by a fellow prisoner who had been moved into his cell a few days earlier. Later in the year, another opposition leader, Olbana Lelisa was reportedly subjected to the same treatment.
  • In September, two Swedish journalists, sentenced in 2011 to 11 years’ imprisonment on terrorism charges, were pardoned. After their release, the two men reported that they were forced to incriminate themselves and had been subjected to mock execution before they were allowed access to their embassy or a lawyer.
Arbitrary arrests and detentions
The authorities arrested members of political opposition parties, and other perceived or actual political opponents. Arbitrary detention was widespread.
According to relatives, some people disappeared after arrest. The authorities targeted families of suspects, detaining and interrogating them. The use of unofficial places of detention was reported.
  • In January the All Ethiopian Unity Party called for the release of 112 party members who, the party reported, were arrested in the Southern Nations, Nationalities and Peoples (SNNP) region during one week in January.
Hundreds of Oromos were arrested, accused of supporting the Oromo Liberation Front.
  • In September, over 100 people were reportedly arrested during the Oromo festival of Irreechaa.
Large numbers of civilians were reportedly arrested and arbitrarily detained in the Somali region on suspicion of supporting the Ogaden National Liberation Front (ONLF).
The authorities continued to arbitrarily detain UN employee, Yusuf Mohammed, in Jijiga. His detention, since 2010, was reportedly an attempt to get his brother, who was suspected of links with the ONLF, to return from exile.
Between June and August, a large number of ethnic Sidama were arrested in the SNNP region. This was reportedly in response to further calls for separate regional statehood for the Sidama. A number of arrests took place in August around the celebration of Fichee, the Sidama New Year. Many of those arrested were detained briefly, then released. But a number of leading community figures remained in detention and were charged with crimes against the state.
There were reports of people being arrested for taking part in peaceful protests and publicly opposing certain “development projects”.
Excessive use of force
In several incidents, the police were accused of using excessive force when responding to the Muslim protest movement. Two incidents in Addis Ababa in July ended in violence, and allegations included police firing live ammunition and beating protesters in the street and in detention, resulting in many injuries. In at least two other protest-related incidents elsewhere in the country, police fired live ammunition, killing and injuring several people. None of these incidents was investigated.
  • In April, the police reportedly shot dead at least four people in Asasa, Oromia region. Reports from witnesses and the government conflicted.
  • In October, police fired on local residents in Gerba town, Amhara region, killing at least three people and injuring others. The authorities said protesters started the violence; the protesters reported that police fired live ammunition at unarmed people.
Security forces were alleged to have carried out extrajudicial executions in the Gambella, Afar and Somali regions.
Conflict in the Somali region
In September, the government and the ONLF briefly entered into peace talks with a view to ending the two-decade long conflict in the Somali region. However, the talks stalled in October.
The army, and its proxy militia, the Liyu police, faced repeated allegations of human rights violations, including arbitrary detention, extrajudicial executions, and rape. Torture and other ill-treatment of detainees were widely reported. None of the allegations was investigated and access to the region remained severely restricted.
  • In June, UN employee Abdirahman Sheikh Hassan was found guilty of terrorism offences over alleged links to the ONLF, and sentenced to seven years and eight months’ imprisonment. He was arrested in July 2011 after negotiating with the ONLF over the release of two abducted UN World Food Programme workers.
Forced evictions
“Villagization”, a programme involving the resettlement of hundreds of thousands of people, took place in the Gambella, Benishangul-Gumuz, Somali, Afar and SNNP regions. The programme, ostensibly to increase access to basic services, was meant to be voluntary. However, there were reports that many of the removals constituted forced evictions.
Large-scale population displacement, sometimes accompanied by allegations of forced evictions, was reported in relation to the leasing of huge areas of land to foreign investors and dam building projects.
Construction continued on large dam projects which were marred by serious concerns about lack of consultation, displacement of local populations without adequate safeguards in place, and negative environmental impacts.

የስምንት ሚኒስትሮች ሹመት ሰሞኑን ይፀድቃል .......የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ዛሬ ግምገማ ያካሂዳል

የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ዛሬ ግምገማ ያካሂዳል
የኢህአዴግ 36 ከፍተኛ መሪዎችን ያካተተው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አመታዊ ግምገማ ለማካሄድ ዛሬ የሚሰበሰብ ሲሆን የስምንት ሚኒስትሮች ሹም ሽርና ሽግሽግ በሚቀጥለው ሳምንት ለፓርላማ ቀርቦ እንደሚፀድቅ ይጠበቃል፡፡ ለሹመት የሚቀርቡት ባለስልጣናት፤ የፍትህ ሚኒስትር፣ የከተማና ኮንስትራክሽን ልማት ሚኒስትር፣ የግብርና ሚኒስትር፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር፣ የገቢዎች ሚኒስትር የደህንነትና መረጃ ሚኒስትር፣ የደንና አካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር እንዲሁም በፓርላማ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ናቸው ተብሏል፡፡ አንዳንዶቹ ሹምሽር እርምጃዎች ሲሆኑ፤ አንዳንዶቹ ደግሞ ወደ አዲስ አበባ አስተዳደር እንዲዛወሩ በተደረጉ ባለስልጣናት ምትክ የሚካሄድ ሽግሽግ ነው፡፡
ይሁን እንጂ የእጩ ተሿሚዎችን ማንነት ለማወቅ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም፡፡ ዛሬ የሚካሄደው የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ ከሹምሽሩ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ቢታሰብም፣ የሰብስባው ዋና ርዕሰ ጉዳይ አመታዊ ግምገማና አመታዊ እቅድ እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት አስፈፃሚ አካል የመቆጣጠር ስልጣን ያለው የአገሪቱ ፓርላማ ጠንካራ የቁጥጥር ሃላፊነቱን በተግባር ማሳየት እንደጀመረ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጭምር ቢናገሩም፤ በሚኒስትሮች ሹመት ዙሪያ ግን የቀድሞው አሰራር አልተሻሻለም፡፡ በተለያዩ ዲሞክራሲያዊ አገራት ውስጥ የእጩ ሚኒስትሮች ማንነት በይፋ ታውቆ ለበርካታ ሳምንታት በፓርላማና በዜጐች ዘንድ ውይይት የሚካሄድበት ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ ግን የተሿሚዎች ማንነት የሚገለፀው ሹመታቸው በሚፀድቅበት እለት ነው፡፡
የስራ አስፈፃሚው ኮሚቴ ዛሬ ስብሰባ እንደሚያካሂድ የገለፁት የኢህአዴግ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን፤ የስብሰባው ዓላማ የዓመቱን የስራ አፈፃፀም በመገምገም ድርጅቱ በኪራይ ሰብሳቢነት ላይ የሚያካሂደውን ትግል አጠናክሮ ለመቀጠል በእቅዶች ላይ መወያየት ነው ብለዋል፡፡ የህዝቡን ተጠቃሚነትና ተሳትፎ በማጐልበት የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትን፤ የህዝብ፣ የመንግስትና የድርጅት አቋሞች እንዲጠናከሩ፣ ችግሮች ያሉባቸውን ደግሞ አንጥሮ ለማውጣት ያለመ ስብሰባ ነው ብለዋል፡፡ በነባር ፖሊሲዎችና አሰራሮች ላይ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው መክሮባቸው አቋም ከወሰደባቸው በኋላ፤ የማስፋት፣ የማጠናከርና የማጐልበት እንዲሁም ተጨማሪና አዳዲስ ዝርዝር የአሰራር አቅጣጫዎችን በመተለም በመጪው አመት እቅድ ላይ ውሳኔ ያሳልፋል ብለዋል - አቶ ሬድዋን፡፡
 
addis adimas
 

ወይዘሮ አዜብ እና ”ለመንግስት ተመላሽ ሊደረግ የነበረ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000)

ወይዘሮ አዜብ እና ”ለመንግስት ተመላሽ ሊደረግ የነበረ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000)

qw
ስብሃት ነጋ …ህዝብን የሚያደነቁሩትን እነበረከትንና የጋሪ ፈረስ የሆኑት ሃ/ማሪያምን እርቃናቸውን አስቀሩ::
ሽማግሌውን በቅርብ የሚያውቋቸው የፓርቲው ሰዎች « ስብሃት ከበረሃ ጀምሮ በቀለኛ ነው። ጥርሱ ውስጥ የገባን ሰው ካላስወገደ እንቅልፍ አይወስደውም፤ ብዙ ሰው አጥፍቶዋል። አሁንም አዜብን እግር በእግር የሚከታተለው ለዚሁ ነው» ይላሉ።
አባተ ኪሾ ከደቡብ ባጀት ተመላሽ የሆነ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000) ለመንግስት ተመላሽ ሊያደርጉ ሲሉ …« ወዲህ በል..የምን መንግስት ነው?» በማለት ተቀብለው ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን አባተ ፍ/ቤት ጭምር ያጋለጡት ነው። ስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ደግሞ ታምራት ላይኔ በውሸት እንዲመሰክር አምስት ጊዜ አግባብተውት እንቢ ሲል ከማስደብደባቸው በተጨማሪ ሌላ ክስ እንዲመሰረትበት አድርገዋል። አቃቤ ሕግ የነበረው ዮሃንስ ወ/ገብርኤል የነስብሃትን የውሸት ክስ ተቀብዬ ተግባራዊ አላደርግም፤ ህሊናዬ አይቀበለውም .. በማለቱ ብቻ ለአምስት አመት እንዲታሰር አላደረጋችሁም?…ብዙ ማስረጃና መረጃ መደርደር ይቻላል።..
ሽማግሌው ስብሃት ነጋ ከጥቂት ቀናት በፊት በሰጡት ቃለ-ምልልስ አስበውት ይሁን ሳያስቡት “እውነት” አምልጧቸዋል። አጥብቀው ያነሷቸው የሙስና ጉዳዮች ራሱን የቻለ « አላማና ግብ » አላቸው። የመጀመሪያው በፓርቲያቸው ውስጥ ያለው ክፍፍል (የጥቅም) እንደተዳፈነ እሳት ውስጥ ለውስጥ እየተብላላ መሆኑን በግልፅ ያሳያል። ከተናገሩት የሚከተለውን እንመልከት፤ « .በጤናማ ሁኔታ የሚገኙ ሰዎችን እንቆርጣለን፣ እናስራለን ወዘተ እያሉ ሲያስፈራሩ የነበሩ የፖለቲካ፣ የመንግስት ሰዎች ነን የሚሉ የፀጥታና የስነ አእምሮ ሁከት ፈጥረዋል። መቶ ሚሊዮን የሰረቁና ያስዘረፉ፣ 10ሺህ ብር የሰረቀውን ሲያገላብጡት ያታያሉ። » ብለዋል። « እንቆርጣለን » ያሉት መለስ ዜናዊ ናቸው፤ መለስ በአደባባይ ይህን ከመናገር አልፈው ሲያስፈራሩም እንደነበር እናስታውሳለን። መለስ ያንን ያሉት በ10ሺዎች የሚገመት ቡና ከመጋዘን ጠፋ በተባለበት ወቅት ነው። ያንን ቡና የሰረቁትና ባህር ማዶ ሸጠው ገንዙቡን ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ምንጭ ተጠቅሶ ይፋ ተደርጓል። እናም ስብሃት “መቶ ሚሊዮን የሰረቁ..» ያሉት አዜብ መስፍንን ሲሆን፣ « ያስዘረፉ» ያሉት ደግሞ ባለቤታቸው አቶ መለስን ነው። « 10ሺህ የሰረቁ..» የተባሉት በቅርቡ የታሰሩት የጉምሩክ ሰዎችን ሲሆን..እነዚህን በንፅፅር ያስቀመጡት የአዜብ (ተላላኪዎች) ስርቆት መጠነሰፊ መሆኑን ለማመላከት ነው። ስብሃት እስካሁን አድፍጠው ቆይተው በዚህ ሰሞን ይህን መናገራቸው ..«አዜብ የከተማዋ ም/ል ከንቲባ ይሆናሉ» የሚባለውን በመስማታቸው ሆን ብለው ያደረጉት ነው፥ ይላሉ ታዛቢዎች።
« ሙስና ከተነሳ ስብሃትም እስከአንገቱ ተነክሮበታል። በገርጂና ሳር ቤት የሚገኘው በአሜሪካ በሚኖሩ ስጋ ዘመዶቹ ስም እንዲሁም በቀድሞ የአየር ሃይል ጄ/ል ሰሎሞን ስም የሚንቀሳቀስ ግን የስብሃት የግል ንብረት መሆኑን የማይታወቅ መስሎት ነው?….ጎንደር -ሑመራ ያለው የሰሊጥ እርሻ የስብሃት አይደለም?…በ10ሚሊዮን ብር በሚገመት በመቀሌ (አፓርታይድ መንደር) ስብሃት ዘመናዊ ቪላ እንደሚገነባ አይታወቅም ብሎ ይሆን?…» ሲሉ እነዚህ ወገኖች የስብሃትን ሙስና በከፊል ይጠቅሳሉ።
ስብሃት በዚህ አላበቁም፤ « ..እስካሁን ከፍተኛ ሙሰኞች ትንሹን ሙሰኛ ከሰው አሳስረው ያስፈርዱና ያሰቃዩ ነበር ይባላል። ከፍተኛ ሙሰኞች ከመርማሪው ጀምረው አቃቤ ሕጉም ዳኛው፣ ምስክሩም ይቆጣጠራሉ። ትንሽ የሰረቀም ምንም ያልሰረቀም ሲሰቃዩና ሲያደኸዩ የነበሩም፤ አሉም ይባላል። ስልክ እየደወሉም ይፈርዱ ነበር ይባላል።» ብለው አረፉት ስብሃት። ትክክል ናቸው!! ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ « ይህን ካልፈረድሽ በመኪና ገጭተን ነው የምንገድልሽ » ተብላለች። ያውም ከቤተ መንግስት ተደውሎ።
አሁን ስብሃት ተናገሩት እንጂ…ህዝቡ ብሎ-ብሎ የታከተው ነገር ነው!! እነ እስክንድር፣መሃመድ አቡበከር፣ አንዷለም አራጌ፣ ርእዮት አለሙ….ወዘተ በርሶ ጓደኞች በስልክ ትእዛዝ የተፈረደባቸው ናቸው!!… «ፍትሃዊ ስርአትና መንግስት አለ..» እያሉ ህዝብን የሚያደነቁሩት እነበረከትና የጋሪ ፈረስ የሆኑት ሃ/ማሪያም እርቃናቸውን የሚያስቀር ነገር ነው በስብሃት የተቀመጠው።

በክልል ከተሞች ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞአቸውን አሰሙ

በክልል ከተሞች ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞአቸውን አሰሙ

ሰኔ ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና :-በአዳማ በአቡበክር መስጊድ በተካሄደው ተቃውሞ ሙስሊም ኢትዮጵያውያኑ ” መንግስት ድምጻችንን ይስማ፣ በሀሰት ክስ አንገዛም፣ አሸባሪዎች አይደለንም” የሚሉና ሌሎችንም መፈክሮች አሰምተዋል። በአሳሳ ከተማም እንዲሁ በአል ከራም መስጂድ ተቃውሞ መካሄዱን ለማወቅ ተችሎአል። በወልድያም እንዲሁ ሙስሊሙ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አሰምተዋል።
በሁለቱም ቦታዎች የተካሄዱት ተቃውሞዎች በሰላም ተጠናቀዋል። መንግስት የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን ከእስር በመፍታት ለሙስሊሞች ጥያቄ መፍትሄ እንዲሰጥ ከፍተኛ ጫና ቢደረግበትም፣ አቋሙን የሚቀይር ሆኖ አልተገኘም። ዘወትር አርብ የሚደረጉ ተቃውሞዎችን መንግስት አሸባሪዎች የሚያቀናብሩት ነው በማለት ተደጋጋሚ መግለጫ ሲሰጥ ቆይቷል።

በአዲስ አበባ ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ምዝገባ የተመዘገበው ህዝቡ ቁጥር መንግስት በቅርቡ ካወጣው አዲስ አበባ ህዝብ ቁጥር ጋር የማይጣጣም ነው ሲሉ አንድ ባለሙያ ገለጹ

በአዲስ አበባ ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ምዝገባ የተመዘገበው ህዝቡ ቁጥር መንግስት በቅርቡ ካወጣው አዲስ አበባ ህዝብ ቁጥር ጋር የማይጣጣም ነው ሲሉ አንድ ባለሙያ ገለጹ

ሰኔ ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና :-በማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ የሕዝብ ቆጠራ ኮምሽን ሰሞኑን የአዲስ አበባ ህዝብ ቁጥር 2 ሚሊዮን 900 ሺ መሆኑን ቢገልጽም፣ በ10 – 90 እና በ20 – 80 እየተባለ በሚጠራው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ የተመዘገበው ህዝብ ቁጥር ኤጀንሲው ያቀረበው አሀዝ  ትክክል አለመሆኑን የሚያሳይ ነው በማለት አንድ ስማቸው እንዳይገለጥ የጠየቁ ቀድሞ በመስሪያ ቤቱ ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ባለሙያ ለኢሳት የአዲስ አበባ ዘጋቢ ገለጹ።
ባለሙያው እንዳሉት በአሁኑ ጊዜ መንግስት ከ800 ሺ እስከ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ነዋሪዎች ለቤት ፍለጋ እንደሚመዘገቡ ከገለጸ የከተማዋ ነዋሪ የዚህን አሃዝ ከ4 እስከ 5 እጥፍ ሊሆን ይችላል ማለት ነው ብለዋል።
መንግስት እስከሁን ከ700 ሺ ህዝብ በላይ እንደተመዘገበ፣ በሚቀጥሉት ቀናትም ተጨማሪ 100 ሺ ህዝብ ሊመዘገብ እንደሚችል መግለጹን ያወሱት ባለሙያው፣ ቀደም ብሎ ቤት ያላቸው ሰዎች ቁጥር ከ300 እስከ 600 ሺ የሚገመቱ ከሆነ በአጠቃላይ በከተማው ከ1 ሚሊዮን 100 ሺ እስከ 1 ሚሊዮን 400 ሺ ሰዎች ቤት ይፈልጋሉ ማለት ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ነባራዊ ሁኔታ አንድ ሰው ከ3 እስከ 4 ልጆች ሊኖሩት እንደሚችል የገለጹት እኝህ ባለሙያ በዚህ ስሌት መሰረት የከተማው ህዝብ ቢያንስ ከ3 ሚሊዮን 500 እስከ 5 ሚሊዮን 500 ሺ ሊደርስ ይችላል ብለዋል።
አሀዙ በቤት ምዝገባ ያልተካተቱትን እጅግ ደሀ የሆኑትን የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም አድራሻ አጥተው የተቀመጡትን ነዋሪዎች ካካተተ ከተማው ህዝብ ብዛት ከ5 ሚሊዮን ሊበልጥ እንደሚችል ገልጸዋል።
የአዲስ አበባ መስተዳድር የከተማውን ህዝብ ቁጥር ከ5 ሚሊዮን በላይ አድርጎ ማቅረቡ ትክክል ሊሆን እንደሚችል፣ ስህተቱ ያለው ማእከላዊ ስታትስቲክስ ባወጣው መረጃ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
የህዝብ ቁጥርን መቀነስ ለምን አስፈለገ የተባሉት ባለሙያው አንዱ ምክንያት በመስሪያ ቤቱ አቅም ችግር ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው ፖለቲካዊ ምክንያት ሊኖረው ይችላል ሲሉም አክለዋል። ክልሎች የፌደራል መንግስቱን የገንዘብ ድጎማ የሚያገኙት በህዝባቸው ቁጥር መጠን በመሆኑ ትክክለኛ የህዝብ ቁጥር ካልታወቀ በማህበራዊ አግልግሎት አሰጣጥ ላይ ችግር ሊፈጥር እንደሚችል አስረድተዋል።

የናይል ተፋሰስ ሚኒስትሮች ተሰበሰቡ [voa]


የናይል ተፋሰስ ሚኒስትሮች ተሰበሰቡ [voa]

ባለ አምስት ቢሊየን ዶላር መዋዕለ-ነዋዩ ኅዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን ጎረቤቶች ቀልብ አነቃቅቶና ውዝግቦችም እየተሰሙ ባሉበት ሁኔታ ውስጥ በአባይ ውኃ አጠቃቀም ላይ ለመምከር የአባይ ተፋሰስ ሃገሮች ድርጅት ስብሰባ ደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ላይ ዛሬ ተሰብስበዋል፡፡

የኅዳሴ ግድብ ወደ ግብፅ የሚወርደውን ውኃ መጠን ይቀንስብናል ሲሉ ግብፃዊኑ ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ ሥጋታቸውን በየጊዜው እየገለፁ ነው፡፡

የኢትዮጵያ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር አቶ አለማየሁ ተገኑም ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ የጀመረችውን ግድብ ግንባታ ሥራ እንደማታቆም አስታውቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የማንንም ሃገር የመሻሻል ዕድል እንደማትቃወም የተናገሩት የግብፅ የውኃ ኃብቶች ምክትል ሚኒስትር አሕመድ ባህ ኤልዴይን ይሁን እንጂ ናይል ወንዝን በተመለከተ ማንኛቸውም ዕቅዶች ከመነደፋቸው በፊት መዘዞች ሁሉ ግምት ውስጥ ሊገቡ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡


ኢሳት የግንቦት 7 ነው?! ( ኢሳት – ጥያቄዎች – በደረጀ ሀብተወልድ)


Ethiopian Satellite Television, ESAT TV

በደረጀ ሀብተወልድ
ከሁለት ሣምንት በፊት ሲቪሊቲ ፓልቶክ ባዘጋጀው የጋዜጠኞችና የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶች ውይይት ላይ ኢሣትን በመወከል ተሳትፌ ነበር። በክፍሉ ታዳሚ ከነበሩት ከ 500 በላይ ተሳታፊዎች መካከል በጣም የሚበዙት የኢሳት ደጋፊዎች መሆናቸውን ሳይ ደስታ ሳይሰማኝ አልቀረም። ከደስታው ባሻገር የተሰማኝ ሌላ ስሜት ግን፦” ሰው እንደዚህ ሲደግፋችሁ፤ የበለጠ በርትቻችሁና ጠንክራችሁ  መሥራት አለባችሁ” የሚል አደራዊ ሸክም ነው።
ደጋፊዎቻችን የመብዛታቸውን ያህል ታዲያ ከጥቂት ሰዎችም ቢሆን  ቅሬታ አዘል ጥያቄዎች መሰንዘራቸው አልቀረም።ኢሳትን በተመለከተ የተሰነዘሩት እነዚህ ተያያዥነት ያላቸው ጥያቄዎች ሲጨመቁ፦” ኢሳት የግንቦት 7 ነው፣ ግንቦት 7 እና መሪዎቹ  ከሌሎች ፓርቲዎች በተለየ ሰፊ የሚዲያ ሽፋን ያገኛሉ፣ ጭራሽ የሚዲያ ሽፋን የማትሰጧቸው ፓርቲዎች አሉ” የሚሉ ናቸው።
ለሦስቱም ጥያቄዎች ለመስጠት የሞከርኩትን መልስ ነው እዚህ  በመልኩ ለማስቀመጥ የሞከርኩት፦
1-      ኢሳት የግንቦት 7 ነው የሚለውን በተመለከተ፦
ይህ ጥያቄ መነሳት የጀመረው ከኢሳት ምስረታ ጊዜ አንስቶ መሆኑ ይታወቃል።በወቅቱ ይህን ወሬ ከሰሙት መካከል  አርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ አንዱ ነበር። ታማኝ  የኢሳት 1ኛ ዓመት በዋሽንግተን ዲሲ ሲከበር ለጥያቄው መልስ የሰጠው፦” አይደለም እንጂ ቢኾንስ !?”በማለት ነበር። ቀደም ባሉት ዓመታትም ራዕይ ያላቸው አገር ወዳድ ዜጎች የቤት ካርታቸውን ሳይቀር እያስያዙ ከባንክ በተበደሩት ገንዘብ ያቋቋሙት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ኔትወርክ(ኢቲኤን) ይሰኝ የነበረው ተወዳጅ   የቴሌቪዥን ጣቢያ “አንዴ የ ሲ. አይ. ኤ ነው ሌላ ጊዜ የ እነ እገሌ ነው” ከሚል ሀሜት ሊያመልጥ ያለመቻሉን ታማኝ በማውሳት፤ ሰው እየወጣ ለሚናገርበትና ሀሳቡን ለሚገልጽበት  ጣቢያ ህልውና-  የድጋፍ ጥያቄ ሲቀርብለት ምላሽ ባለመስጠቱና የጣቢያውን ህልውና ማስቀጠል ከነዛ ጥቂት ሰዎች አቅም በላይ በመሆኑ ሊዘጋ መቻሉን አብራርቷል።
“በጣም የሚያሳዝነው ኢ.ቲ.ኤን ተዘጋ ሲባሉ  እሠይ! ደግ ሆኑ!” ያሉ ሰዎች መሰማቱ  ነው።”ሲልም ታማኝ አክሏል።አዎ!ጣቢያው መዘጋቱ የሁሉም መናገሪያ አፍ መዘጋቱ ቢሆንም፤ በዚህ የተደሰቱ  <<ሰዎች>> እንደነበሩ ታማኝ ልምዱን አካፍሎናል።
በወቅቱ ኢሳት በአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ መሆኑን የገለጸው ታማኝ፤ ይህን እውነት የማይቀበሉ- የማንም ይሁን የማን የባለቤትነቱ ጉዳይ ሊጨንቃቸው እንደማይገባ፣ ኢሳትን ሊጠይቁትና ሊተቹት የሚገባው እየሠራው ባለው ሥራ ሊሆን እንደሚገባው፣ የዚህ ዓይነት ሥራ የሚሠራ ሚዲያ አይደለም ግንቦት 7- ኢህአዴግም ቢሆን ካቋቋመ ሊመሰገን እንጅ ሊነቀፍ  እንደማይገባው በመንገር ነበር ምላሹን የቋጨው።
-የዩኒቲ ኮሌጅ ባለቤትና ፕሬዚዳንት በነበሩት በዶክተር ፍስሀ እሸቱ “ዕለታዊ አዲስ” የተሰኘ ዘወትር የሚታተም ጋዜጣ ሲቋቋም በፕሬስ ተቋሙ ታቅፈው ከሠሩት ጋዜጠኞች መካከል- ይህ ፀሀፊ አንዱ ነበር። ያኔ ዕለታዊ አዲስ ይታማ የነበረው “ሲ.አይ.ኤ ያቋቋመው ነው” እየተባለ ነበር። ጋዜጣው በርዕሰ-አንቀጹ  በሰጠው ምላሽም ፦”አረ በፍፁም! የሲ.አይ. ኤ አይደለሁም”የሚል ሙግት ውስጥ አልነበረም የገባው-ይልቁንም፦ “ሲ.አይ. ኤ ይህን ጋዜጣ፤ እየሠራ ላለው ተግባር አቋቁሞ ከሰጠ ሊመሰገን ይገባዋል” የሚል ነበር ምላሹ።ሁሌም አዲስና ተልቅ ነገር ከትችት  ሊያመልጥ እንደማይችል ያለፉ ልምዶቻችን ሁሉ ምስክሮች ናቸው።
በኢሳት ዙሪያ ለተነሳው ተመሣሳይ ጥያቄም በበኩሌ ከዚህ ውጪ ምላሽ የለኝም። ኢሳት በአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ነፃ ሚዲያ መሆኑን እረዳለሁ።  እኔ የምናገረው፤ የማውቀውን ያህል ነው። ይህን ስነግረው <“አይ ተሣስተሀል ፤ኢሣት የግንቦት 7 ነው”  የሚለኝ ካለ ምላሼ፦”እና? ቢሆንስ?” የሚል ነው።ግንቦት 7ቶች ራሳቸውን የሚተቿው ሰዎች ሰይቀሩ በተደጋጋሚ  የሚስተናገዱበትን ነፃና ገለልተኛ ሚዲያ ካቋቋሙ በእውነት  ልናደንቃቸው ይገባል። አዎ!እንደሚወራው ኢሳት የግንቦት 7 ነው ብለን የምናምን ከሆነ፤ የየግንቦት 7 መሪዎች  ዲሞክራቶች መሆናቸውን በተግባር ከማስረገጥ ውጭ ሌላ የሚሰጠን ትርጉም ሊኖር አይችልም።
2-ግንቦት 7 እና መሪዎቹ በኢሳት የተለየ ሽፋን ያገኛሉ የሚለውን በተመለከተ፦
ይህ አባባል  በመረጃ ላይ ሳይሆን በግምት የተወሰደ ድምዳሜ እንደሆነ ተረድቻለሁ።ግምት ሁልጊዜ ህሊናዊ(ሰብጀክቲቭ) ነው። ይሆናል ብለን የገመትነው ነገር በመረጃ ሲመረመር ከግምታችን ውጪ የሚሆንበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም። ግንቦት 7 ሰፊ ሽፋን ያገኛል የሚለውን ወሬ ለመጀመሪያ ጊዜ  የሰማን ሰሞን ለማወቅ ያህል ” ለየትኛው ፓርቲ ብዙ ሽፋን ሰጥተናል?” በሚል -ዜናና ፕሮግራም ቆጠራ ድረስ ገብተናል።ያኔ አንድነት ፓርቲ ጥሩና ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ የሚያደርግበት ጊዜ ነበር(እነ አንዷለም ሳይታሰሩ ማለቴ ነው)  በወቅቱ ባደረግነው ቆጠራ ሰፊ ሽፋን አግኝቶ የነበረው አንድነት ፓርቲ ነው። ዶክተር ነጋሶ፣ አቶ አንዷለም፣አቶ አስራት ጣሴ… ሌሎችም  የአንድነት አመራሮች በተደጋጋሚ ቃለ-ምልልስ የሰጡበትና ያወጧቸው የነበሩት መግለጫዎች በሙሉ ሽፋን ያገኙበት ጊዜ ነበር።
-ግንቦት 7 በነጀነራል ከማል ገልቹ ከሚመራው የኦነግ አንድኛው ክንፍ ጋር ትብብር በመሰረተ ሰሞን ደግሞ- ከፍ  ያለ ሽፋን አግኝቶ ነበር።
-የሙስሊሞች መብታችን ይከበር ጥያቄ የተነሳ ሰሞን ደግሞ ጉዳዩ ከሁሉም የበለጠ ከፍተኛ ሽፋን አግኝቶ ነበር።
-የዋልድባም እንደ ችግሩ መጠን ሰፊ ሽፋን አግኝቷል።
-ከሳምንታት በፊት ሰማያዊ ፓርቲም እንዲሁ  ትርጉም ያለውና ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ማድረግ ሲጀምር ሰፋ ያለ ሽፋን አግኝቷል። ወዘተ..
-በግለሰብ ደረጃም የዓባይ ወንዝ ግድብ ይፋ መሆኑን ተከትሎ ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እነ ዶክተር ጌታቸው በጋሻው እንዲሁም በአውስትራሊያ፣ በአውሮፓና በደቡብ አፍሪካ የ ኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ ሲያካሂዱ እነ  ታማኝ በየነ፣ በተለያዩ ጉዳዩች ፖለቲካዊ ትንታኔያቸውን እንዲያጋሩን ስንፈልግ  ደግሞ እነ ጃዋር መሀመድ… ወዘተ በተደጋጋሚ በኢሳት ላይ ቀርበዋል። ይህ ማለት ጋዜጠኞቹ ለምንሠራቸው ዘገባዎችና ቃለምልልሶች  በአመዛኙ እየተመራን ያለነው በክስተቶች (Events) ነው ማለት ነው።
አንዳንዶቻችን ግን ይህን አልተገነዘብንም ወይም ላለመገንዘብ አስቀድመን የራሳችንን መስመር አስምረናል። ከተጠቀሱት ድርጅቶችና ግለሰቦች ጎልቶ ሚታየን፤ እነ ዶክተር ብርሀኑ ኢሳት ላይ መናገራቸው ብቻ ነው።እደግመዋለሁ ሁላችንም ሳንሆን አንዳንዶቻችን።
ስለዚህ በዚህ ዙሪያ የምንወቀስበት ነገር ካለ ወቀሳው መቅረብ ያለበት ከላይ በአብነት  እንደተጠቀሱት ያሉ  ትኩረት ሳቢ(የዜና ዋጋ ያላቸውን) እንቅስቃሴዎች አድርጎ ሽፋን ያልሰጠንለት ድርጅት ካለ፤ ያን በማሳየት  ቢሆን ይመረጣል። “ጥሩ አንቀሰቃሴ(የዜና ዋጋ ያለው) አደርጌ ሽፋን አልሰጣች ኝም”የሚል ድርጅት ካለ በተጫባጭ በማሳየት ሊወቅሰንም፣ በአደባባይ ሊከሰንም ይችላል።ያ ሲሆን እኛም ያላየናቸውን ስህተቶች ዐይተን ለማስተካከል ዕድል ይኖረናል።እስካሁን ባለው ሂደት በማንም ይደረጉ በማን፤ ያየናቸውን ክስተቶች በሙሉ ያለምንም አድሎ ባለን አቅምና የሰው ሀይል ለመሸፈን ሞክረናል።ከዚህም አልፎ(ብዙዎቹ መረጃ ለመ ጠት ፈቃደኛ አይሁኑ እንጂ) በተለያዩ ጉዳዩት ዙሪያ የመንግስትን  ሀላፊዎች ለማነጋገር ብዙ ጊዜ ሙከራ ተደርጓል።
ይህን ስል  የተሟላ ሥራ እየሠራን ነው እያልኩ አይደለም።ብዙ በሚሠራ ተቋም አልፎ አልፎ ለስህተት መዳረጉ የሚጠበቅ እስከሆነ ድረስ ፤ ችግሮች ሊኖሩ ይችላሉ። እኛ ራሳችን የምናያቸውና የምንነጋገርባቸውም ነገሮች አሉ።በየጊዜው ግን ድክመቶቻችንን ለማሻሻል ጥረት እያደረግን ነው። አሁንም የምለው ነገር ቢኖር፤  በዚህ ረገድ ድክመቶች ተስተውለውብን ከሆነ፤ልንመከርና ልናስተካክል ዝግጁ ነን።
በ3ተኛ ደረጃ የተነሳውን ጥያቄ የማየውም ከዚሁ አንፃር ነው። እስከዛሬ የሚዲያ ሽፋን ያላገኙ ድርጅቶችና ግለሰቦች ይኖራሉ። ያ የሆነው ቀደም ሲል እንደጠቀስኩት በአመዛኙ በክስተቶች እየተመራን በመሥራታችን እንጂ በሌላ ምክንያት አይደለም። ወደፊት እነዚህን ጉዳዮች በዕቅዳችን በማካተት ያሉብን ጉድለቶች ለማሻሻል እንጥራለን። ኢሳት የኢትዮጵያ ሕዝብ ዐይንና ጆሮ ነው የምንለው ለመፈክር ብቻ አይደለም። ከልብ በማመን ነው።
በመጨረሻም፦
ሰሞኑን  በፌስ ቡክ በተሰራጨው የዶክተር ብርሀኑ ንግግር ዙሪያ አስተያየት እንድሰጥ የጠየቃችሁኝ በርካታ ናችሁ።የተሟላና የጠራ መረጃ ባላገኘሁበት ሁኔታ አስተያዬት መስጠት ስላልፈለግኩ ነበር ዝም ያልኩት። አንዳንዶቻችሁ ግፊታችሁን ባለማቆማችሁ በአጭሩ የምለውን ልበል፦
ዶክተር ብርሀኑ በንግግራቸው የጠቀሷቸው ሁለት ተቋማት አሉ-ግንቦት 7 እና ኢሳት። በሚመለከተኝ በኢሳት ጉዳይ ላይ  ባ’ጭሩ የምለው ነገር ቢኖር ፦የኢሣትን ህልውና  ለማረጋገጥና ቢያንስ አሁን በሚያደርገው መጠን ስርጭቱን ለማስቀጠል  ከተፈለገ ፤ ዲሞክራሲ በአገሬ እንዲያብብ እሻለሁ የሚሉ ግለሰቦችም ሆነ ድርጅቶች ሁሉ ኢሣትን የመርዳት ሀላፊነት ጭምር አለባቸው የሚል ነው። ኢሣት ከምስረታው ድረስ እስካሁን ድረስ “እባካችሁ እርዱኝ” እያለ እንደሚገኝ  በግልጽ የሚታወቅ ነው ።  ይሁንና እንደ ኢሣት ያለን -ከነ ኢቲቪ የተለየ ድምጽን የመጠበቅ  ሀላፊነቱ- የግለሰቦችና የድርጅቶች ብቻ አይደለም።  ስላልታደልን ነው እንጂ በዋነኝነት ኢሣትን  ሊረዳ የሚገባው የኢትዮጵያ መንግስት ነበር።
እዚህ ላይ ሊነሳ የሚገባው ዋነኛ ጥያቄ፦” ኢሳት ከግለሰቦችም ሆነ ከተለያዩ አካላት የሚያገኘው ድጋፍ የኢዲቶሪያል ነፃነቱን አያሳጠውም ወይ?” የሚል መሆን ነው ያለበት። አዎ! የገንዘብ ድጋፍ መቀበልን- የሚዲያን ነፃነትና ገለልተኝነት አሳልፎ ከመስጠት ጋር በማያያዝ ስጋታቸውን የሚገልጹ ወገኖች ሊኖሩ ይችላሉ። ይህ ተገቢ ስጋት ነው።
ይሁንና ኢሣት የተመሰረተበት ጊዜ፣ ቦታ(በስደት)፣ዓላማ፣ የተቋሙ አወቃቀር፣የሚገኝበት ሁኔታ ወዘተ..ለተጠቀሰው ስጋት የሚያጋልጠው አይደለም። ይነስም ይብዛም በተለይ በውጪ አገር የሚገኙ በርካታ  ኢትዮጵያውያን  በቋሚነት ሳይቀር ኢሣትን እየደገፉ ይገኛሉ። እነዚህ ወገኖች ኢሳትን እየደገፉ ያሉት ለራሳቸውና ላ’ገራቸው ሲሉ ነው። የድጋፍ መነሻቸውም ይህ አመለካከታቸው ነው። ሰዎቹ ኢሳትን በቋሚነት ስለሚደግፉ በግላቸው ያገኙት ወይም የተደረገላቸው ነገር የለም።ሊኖርም አይችልም። ድጋፍ የሚያደርጉ ድርጅቶችም ጉዳይ  ከዚህ በተለየ መልኩ ሊታይ አይችልም።አንድ ድርጅት ኢሳትን ሊረዳ የሚገባው የኢሳት መኖር ለማደርገው (ለሚደረገው) ዲሞክራሲን የማምጣት ትግል ጠቃሚ ነው በሚል አመለካከት እንጂ- ባደረገው ድጋፍ ምክንያት በተለየ መልኩ በሚዲያው ለመስተናገድ በማሰብ  አይደለም። ግንቦት 7ትም አንደተበለው አሣትን ደግፎ ከሆነ  ከዚህ እሣቤ ውጪ  ይሆናል ብዬ ፈጽሞ አልገምትም።  “በታገልነው ልክ የስልጣን ደመወዝ ይገባናል “ የሚሉ ገዥዎችን አምርረው የሚኮንኑ ሰዎች ይህን ያስባሉ ማለት በጣም ይከብዳል።     እስካሁን ያሉት የኢሣት አሠራሮችም ይህን አያመለክቱም።
ላብራራ፦  በኢሣት ጋዜጠኞች የኤዲቶሪያል ስብሰባ ላይ አንድም ቀን ከሌሎች በተለየ መልኩ ለእገሌ ፓርቲ ወይም ድርጅት  ይሄ ይሠራለት የተባለበት ጊዜ  ፈጽሞ የለም-ሊኖርም አይችልም።እስካሁን ድረስ የኢዲቶሪያል ነፃነታችን  የተጠበቀ እንደሆነ በድፍረት መናገር እችላለሁ። አልዋሸሁም።ይህን ፅሁፍ  ጓደኞቼ ሊያነቡት እንደሚችሉ አውቃለሁና ቢያንስ እነሱ እንዲታዘቡኝ አልፈልግም።ከዚያም በላይ ህሊና አለ። ማንም ጣልቃ የማይገባበት የኤዲቶሪያል ነፃነት አለን። ሥራችንን እና እንግዶቻችንን የምንወስነው  በኤዲቶሪያል ስብሰባችን  በነፃነት እየተነጋገርን፣እየተከራከርን፣እየተሟገተን ነው።   በምን ምክንያት  ካ’ገራችን ተሰደድን?  …… <<አሳልፈን አንሰጥም!>> በማለታችን ምክንያት ለእስር እና ለስደት የተዳረግንበትንና ስንት ያየንበትን መክሊታችንን/ሀብታችንን/ ነፃነታችንን፤ እዚህ ለምን ብለን የምንጥለው ይመስላችሁዋል? ለገንዘብ? ለጥቅም? ወይስ ለዝና?  በፍጹም!!!  እንዳትሣሳቱ።  ቢያንስ ለራሳችን ክብር  አለን።               ሀቁ ይኸው ነው፦  ነፃና ገለልተኛ የሆነ የኤዲቶሪያል ነፃነት አለን። አምላክ ዕድሜና ጤናውን ይስጠን እንጂ – ይህ ሙያዊ ነፃነታችን ተጠብቆ እስከቀጠለ ድረስ ከኢሣት ጋር እንቀጥላለን።እደግመዋለሁ፦ደመወዝ እስከተከፈለን ድረስ ሳይሆን ፤አሁን ያለን ሙያዊ ነፃነት እስከተጠበቀ ድረስ።    በዚህ አጋጣሚ  እንዲህ ያለ ሙያዊ ነፃነቱ የተጠበቀ የሚዲያ ተቋም ለመሰረቱ ሰዎች ያለኝን ታላቅ አክብሮት ሳልገልጽ ባልፍ፤ ንፉግ እሆናለሁ።
እናም… አስተያዬቴን የጠየቃችሁኝ ሰዎች፣ እንደተባለው ግንቦት 7- ለኢሳት ድጋፍ አድርጎ ከሆነ፤ የግንቦት 7 መሪዎችን- በባልደረቦቼና በኢሳት ወዳጆች ስም ከልብ አመሰግናለሁ ከማለት ውጪ ሌላ ምን ልል እችላለሁ?ሌላ ማለት ካለብኝ ልል የምችለው፦  “ ሌሎችም ድርጅቶች ሆናችሁ ግለሰቦች በምትችሉት አቅም በልጅነት ዕድሜ ላይ የሚገኘውን ኢሳትን በመርዳት በአገራችን  ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ታግዙ ዘንድ አደራ!” ነው ።
ኢሣት የኢትዮጵያ ሕዝብ አንደበት፣ ዓይን እና ጆሮ ነው!!!

Friday, June 28, 2013

በአዜብ መስፍን ላይ ምርመራ እንዲደርግ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ጥያቄዎችህ እየቀረቡ ነው::

Postby
Ethiopia: Azeb Mesfin, EFFORT Employees Vow to Make the Late PM Meles Zenawi’s Vision a Reality
እነመላኩ ፋንታን ተከትሎ በአዜብ መስፍን ላይ የሚቀርቡ የሙስና አቤቱታዎች ጨምረዋል::
የሙስና ኮሚሽን በአቶ ገብረዋህድ ቤት ባደረገው ፍተሻ እንዲሁም ከኣሁን ቀደም በመርማሪ
ደህንነቶች ክትትል በተደረገ የስልክ ጠለፋ የቀድሞ ሟች ጠ/ሚ ባለቤት እና በአለም ትልቁ
የሙስና አባት ኤፈርት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገብረዋህድ ባለቤት እና
እህት ጋር በከፍተኛ ደረጃ የቢዝነስ ስራ ይሰሩ እንደነበር እና ከታሰሩት ባለስልጣናት እና
ባለሃብቶች ጋር የንግድ አጋርነት እንዳላት አረጋግጧል::ይህንን የሚጠቁሙ ሰነዶች እና
ከተለያዩ ወገኖች የሚቀርቡ ጥቆማዎች እና አቤቱታዎች ምርመራው ወደ አዜብ መስፍን
አምርቶ ለጥያቄ እንደምትፈለግ ፍንጭ እየሰጠ ነው ሲሉ የሙስና ኮሚጽሽን የውስጥ አዋቂ
ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::ለሙስና ኮሚሽን ከደረሱት አቤቱታዎች ከፊሎቹ :
-ኤፈርትን ተገን በማድረግ የተለያዩእቃዎችን ካለቀረጥ እያስገባች ነው::
ኤፈርት ለመንግስት መክፈል የሚገባውን ህጋዊየግብርም ሆነ ሌላ ክፍያዎች እንዳይፈጸም አድርጋለች::
ዩዲ ኒሳን ዲዝል ገልባጭ መኪኖችን ካለቀረጥ ነጻ በማስገባት በአቶ ከተማ ከበደ/ኬኬ/ ስም ሸጣለች::
ከዚህ ቀደም እያሱ በርሄ ጋር በኋላም
ከኮሎኔል ሃይማኖት ጋር የተከለከሩ የቴለኮሚኒኬሽን ኬብሎችን
እና ቴክኖሎጊካል የመገናኛ መሳሪያዎችን ካለቀረጥ በማስገባት ሰርታለች::በነጻ ትሬዲንግ በኩል የተለያዩ
ዘመናዊ መኪኖችን ካለቀረጥ እያስገባች በአቶ ነጋ ገ/ዝጌር ስም ትሸጣለች::በሰበታ አለምገና አከባቢ
የአበባ ሰፊ እርሻዎች አላት :: በህገወጥ የዶላር እና የኢሮ ዝውውር ውስጥ መሪ ተሳታፊ ናት::
ባንክ ኦፍ ማሌዥያ እና የሲንጋፖር ባልሃብቶችን እንዲሁን ቻይናውያንን በህገወጥ አለማቀፍ
የገንዘብ ዝውውር ተባባሪ አድርጋ እየሰራች ነው::በተለያዩ አረብ አገራት እና በሃገር ውስጥ
ባስቀመጠቻቸው ደላሎች ኢትዮጵያውያን ሴቶችን በሱዳን እና በየመን አድርጋ ወደ አረብ አገራት ትሸጣለች:
:በተለያዩ የቤተሰብዋ አባላት ስም ባወጣችው የኮንስትራክሽን ንግድ ፍቃዶች ጨረታዎችን በጉልበት ከመቀማት
እየሰራሽ ሲሆን ሌሎች ባለሃብቶችን በስማቸው በመጠቀም የተለያየ ቢዝነሶችን እያካሄደች ነው የሚሉ አቤቱታዎች
እና ጥቆማዎች ለሙስና ኮሚሽን የመርማሪዎች ቡድን ደርሷል::
ይህንን ተከትሎ ጠንካራዎቹ የወያኔ አባላት በወይዘሮ አዜብ መስፍን ላይ ምርመራ እንዲደርግ
ግፊት እያደረጉ ሲሆን ወይዘሮዋ በአሁን ሰአት ራሳቸውን በተለያየ ምክንያት ገኖ ለማውጣት
ላይ ታች እያሉ መሆኑን ታውቋል::

ሰበር ዜና የዩናይትድ ስቴትስ ሴኔት የኢሚግሬሽን ሕጉን አሣለፈ

አሜሪካ ውስጥ ያለ ሕጋዊ ፍቃድና ሰነዶች የሚኖሩ ከአሥራ አንድ ሚሊየን በላይ ሰዎችን ወደ ዜግነት ሊወስድ እንደሚችል የታመነበት የኢሚግሬሽን ማሻሻያ ሕግ በሕግ መወሰኛ ምክር ቤቱ በከፍተኛ ድምፅ አለፈ፡፡
nb
ዋሺንግተን ዲ.ሲ. —
አሜሪካ ውስጥ ያለ ሕጋዊ ፍቃድና ሰነዶች የሚኖሩ ከአሥራ አንድ ሚሊየን በላይ ሰዎችን ወደ ዜግነት ሊወስድ እንደሚችል የታመነበት የኢሚግሬሽን ማሻሻያ ሕግ በሕግ መወሰኛ ምክር ቤቱ በከፍተኛ ድምፅ አለፈ፡፡
በምክር ቤቱ ውስጥ ዛሬ በተሰጠው ድምፅ 68 ሴናተሮች የድጋፍ ድምፃቸውን ሲሰጡ 32 ሴናተሮች ደግሞ ተቃውመውታል፡፡
ይህ ሕግ አያይዞም ዩናይትድ ስቴትስ የተጠናከረ የወሰን ጥበቃ እንዲኖራት የሚያዝዝ ሲሆን ከሜክሲኮ ጋር ባላት ድንበር ላይ ሃያ ሺህ ተጨማሪ የወሰን ቃፊሮች እንዲሠማሩ እና የአንድ ሺህ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው አዲስ አጥር እንዲሠራ ይፈቅዳል፡፡
የተበላሸውን የሃገሪቱን የኢሚግሬሽን ሥርዓት ለመጠገን አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስኬድ ነው ሲሉ የሕጉ ደጋፊ የሆኑት በአፍሪካ ጉብኝት ላይ የሚገኙት ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለዛሬው የሴኔቱ ውሣኔ አድናቆታቸውን ገልፀዋል፡፡
ሕጉ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለተወካዮች ምክር ቤቱ የሕግ መምሪያው እንደራሴዎች ለድምፅ ይቀርባል፡፡
ሕግ ለጣሱ ምህረት የሚሰጥ ነው የሚሉትን ማንኛውንም እርምጃ እንደሚቃወሙ ወግ አጥባቂ ሪፐብሊካኖች ይናገራሉ፡፡
VOA Amharic

postd by Girum K.

ዓባይና የመለስ ዜናዊ (ወያኔ) ታላቁ ሴራ! በከፋለ


ሰሞኑን የአለምንና የኢትጵያውያንን ሀሳብና አስተየት ለመለዎጥ ወይም ለማሳሳት ወያኔ በወኪሎቹ አማካይነት የተለመደዉን ፕሮፓጋንዳ ሲነዛ ከርሞአል። ዓባይ እንደሚጠቅመን ሆኖ ቢገደብልን እጂግ ደስ ይለን ነበር። የወያኔ ትግሬዎች ሰለአባይ ከባለቤቱ ከኢትጵይያ ህዝብ በላይ የሚያቀነቅኑበት የሚጮሁበትና ሚያስመስሉበት ምክንያቱ ሌላ ነው። እነሱ ሃገር ወዳድ ሌሎች ኢትዮጵዉያን ሀገራቸዉ ብታድግና ብትጠቀም የሚጠሉ ሆነው አይደለም።
የኢትዮጵያም ህዝብ ይህንን በደንብ ያዉቀዋል። ከእባብ እንቁላል እርግብ ኣልጠብቅም ብሎአቸዋ። ታዲያ ይኸ ሁሉ የአዞ እንባ ማፍሰስና የኢትዮጵያን ሀዝብ ጩኸት ለመቀማት የመሞከር ሚስጥሩ ምንድነው??? ወያኔ ኢትዮጵያን ለመጉዳትና ለረጂም ጊዜ እችግር ዉስጥ ለማስገባት ካስጠናቸዉ ትልልቅ ጉዳዮች (ፕሮጀችቶች) ኣንደኛዉና ዋናው የአባይ ግድብ ነው። ለዚህም ማስረጃ የሚከተሉትን ነጥቦች ተመልከቱ:
ሀ) ግድቡ የሚሰራው በጥንቃቄ የመሀል ሀግሩን ህዝብ በተለይም አማራዉንና ኦሮሞዉን እንዳይጠቅም በጣም እርቆ በጠረፍ ላይ ነዉ። ይህም በተለይ አማራዉና ሌሎች በአካባቢው የሚኖሩ ህዝቦች በምንም አይነት ለእርሻ (ለመስኖ) ለመጠጥ ለኢንዱስትሪና ለኤሌክትሪክ ኣገልግሎት እንዳይጠቀሙ ታስቦ የተሰራ ነው።
ለ) ሁለተኛዉ የተንኮል አካል ይኽ ጥቅም የማይሰጥ ነገር ግን ሆን ተብሎ በኣካባቢዉ ግጭት እንዲነሳና በዚያ ጥቅም በሌለዉ ግድብ ክዚህ በፊት በሺራሮና በባድመ ላይ እንደተደረገዉ ሁሉ የኢትዮጵያዉያንን ደም በማፍሰስና እነሱ እየዘረፉ ለመኖር የዘረጉት ወጥመድ ነው። ግድቡ ከፍ ብሎ ከተሰራ ወደ ሌሎች ኣካባቢዎች ወደ ምስራቅና ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ተዘርግቶ ሌሎች የሀገሪቱ ኣካሎች ይጠቀሙ ነበር ። ነገር ግን ያ ባለመፈለጉ የግድቡ ስራ ኤሌክትሪክ ለሱዳንና ለግብጽ ማመንጨትና መሽጥ ብቻ ሲሆን የተመረጠዉም ቦታ እድንበር ኣካባቢ ነው:: ይህም በመሆኑ ድንገት ግጭት ቢከሰት እድንበር ላይ በመሆኑ በግብጽም ሆነ በሱዳን በቀላሉ የሚመታና የሚመክን ነዉ። ልክ ወደ ትግሬ የባቡር ሃዲዱ ሲዘረጋ አማራዉንና ኦሮሞዉን አግልሎ ወይም ሳይነካ ከአዋሽ ተነስቶ ዳር ዳሩን እየዞረ በአፋር በረሀ እንደ ደጋን ጎብጦ ከተጉአዘ በሁዋላ ወደ ቀኝ በመታጠፍ የትግሬ ከተሞችን አዳርሶ እንደቆመው የባቡር መንገድ አይነት መሆኑ ነው።
ሐ) ሶስተኛዉ ትልቁ የሴራው አካል በአባይ ግድብ ስም እጂግ ግዙፍ የሆነ የኢትዮጵያ ሀዝብ ገንዘብ በህጋዊ መልክ መዝርፍና ማደህየት ነው። በዚህ ግዙፍ የዝርፊያ ስልት በኑሮ ውድነት ላይ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች አርሶ ኣደሮች ነጋዴዎችና ሌሎች የህበረተሰብ ክፍሎች ካፋቸዉ እየተነጠቁ ለኢትዮጵያ ህዝብ ለማይጠቅምና በራሳቸዉ ላይ ችግር ለሚፈጥር ሰራ እየተበዘበዙ (እየገበሩ) ነው። በሌላ በኩል በጣም የሚያሳዝነዉ ወያኔዎች የዘርፉትና በግልጽ አለም ካወቀዉ ገንዘብ ዉስጥ 3 .00 ቢሊዮን በመለስ ሰም የተቀመጠ ሲሆን 11.70 ቢሊዮኑ ደግሞ ከኢትዮጵያ ውስጥ በህገወጥ መንገድ ተዘርፎ የሽሸ ነው። ይህ ማለት ወያኔወች የዘርፉት ገንዘብ ብዛት አራት የአባይ ግድቦችን ሊያሰራ የሚችል በመሆኑ ኢትዮጵያ በመድማት ላይ መሆኑዋን የዉጭ ሚዲያዎ በግልጽ ጽፈዋል።
መ) ሌላዉ ኣስገራሚ ሚስጥር አልጃዚራ ላይ ከግብጽ ከኢትዮጵያና ከእንግሊዝ አገር ተጋብዘው በተደርገው ዉይይት ላይ ግብጻዊቱዋ እዲህ ብላለች ” ግድቡ ሀገራዊ (ናሽናል) ሳይሆን ክፍለ አሁጉራዊ (ሪጂናል) መሆኑን ሙዋቹ መለስ ዜናዊ ተስማምቶበታል” በማለት የዎያኔዉ መሪ ክህደት መፈጸሙን አጋልጣለች (ይህንን ታሪካዊቪዲዮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ማየት ኣለበት)። ይህም ማለት የግደቡ ባለቤቶች ሱዳን ግብጽና ሌሎች በአካባቢዉ የሚገኙ ሀገሮች ጭምር ናቸዉ ማለት ነው::
ከዚህም አልፎ ተርፎ ዜጎች መሰዋእትን ከፍለዉ ባቆዩዋት ሀገር ዉስጥ መብታቸዉን በመጠየቃቸዉ ብቻ በጸራራ ጸሃይና በድብቅ ሲገደሉ የዘር ማጥፋት ዘመቻ እያካሄዱ ወገኖቻችንን ከሚኖሩበርት ቦታ በግፍ እያፈናቀሉ የነጻነት ታጋዮችን እያሳደዱ እየደበደቡ እያሰሩና እያሰቃዩ ለህዝቡ ጠላት ከመግዛት በስተቀር ለእድገት ለማይጠቅም ግድብና በአባይ ስም ለኢትዮጵያ አሳቢ መስሎ ለመታየት እየሞከሩ ነው። ፕሮጀክቱ ሲነደፍ በጥላቻና ግዙፍ ገንዘብ ለመዝረፊያ በመሆኑ በአጠቃላይ ኢትዮጵያዉያንንና በአባይ ተፋሰስ አካባቢ ኑዋሪ የሆነውን ሰፊ ሕዝብ አላማከሩም። ህዝቡም ሃሳቡን ተጠይቆ አልተሳተፈበትም።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ወያኔ ለአንተ በታሪክ ዉሰጥ ጥሩ አስቦም ሆነ ሰርቶ ስለማያዉቅ በምትወደዉ ወንዝሕ በአባይ ሽፋን የተጋረጠብህን ተንኮል በጣጥሰህ ወያኔን በማስወገድ በሚጠቅምህ መልኩ አባይንና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችህን ወደፊት ለመገንባት ስለምትችል አሁን ወያኔ በሚነዛው የዉሸትና ፕሮፓጋንዳ እንዳትረታ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

postd by Girum K

በካይሮ የኢትዩጲያ ስደተኞች ማህበር የአደጋ ጊዜ መከላከያ ግብረ ሃይል የወጣ መግለጫና ማስጠንቀቅያ



0
bb
በ 30-6-2013 በሀገሪቱ ላይ በሚደረገው ሰለፍ ተነሳ ነገሮች ከቁጥጥር ውጭ ወጥተው በስደተኛው ላጭ ወጥተው በስደተኛው ላይ አደጋ ሊፈጥር እንደሚችል በቀጥታ የስደተኛው ጉዳይ የሚመለከተው የ UNHCR የስደተኞች ጉዳይ ቢሮ ያወጣውን መግለጫ ማስነበባችን ይታወሳል። ይህ ባኢነዲህ እንዳለ ሌላኛው ከስደተኛው ጋር ግንኙነት ያለው የካሪታስ ቢሮ የችግሩን አደገኛነትና አሳሳቢነት በማመን የራሱነ መግለጫ ከማውጣቱም በላይ ቅድመሁኔታዎችን አስቀምጡአል በዚህም የተነሳ ማህበሩ ከስራ አስፈጳሚው ከሪጂናልና ከህብረተሰቡ ውሰጥ ተመረጡ አባላትን በማደራጀት ስደተኛውን ለመታደግ በዘመቻ መለክ የስራ እንቅስቃሴ ጀምርዋል።
በዚህም መሰረት ስደተኛው በማንኛውም ጊዜና ቦታ ችግር ቢገጥመው በየሰፈሩ በተዋቀረው ግብረሃይል አማካኝነት በቀጥታ በተከፈተው ስልክ በመደወል አፋጣኝ እርዳታ የሚያገኝ ከመሆኑም በላይ ማህበርተኛው በዜጎች ላይ የደረሰውን ችግር በዚህ ስልክ በመደወል ማሳወቅ ይኖረበታል፦–
መስር አል ጀዲዳ ለሚኖሩ……ቁጥር 1- ባልቻ-01001820761
ቁጥር 2- ባልቻ- 01224935746
መሃነድሲን ለሚኖሩ……..ቁጥር 1- ጎራው-01206239287
ቁጥር 2-ጎራው-01151423038
ማዓዲ ለሚኖሩ………………ቁጥር 1-ዛጎል-01153018903
ቁጥር 2-ዛጎል-01001521972
በመደወል አገልግሎት ማግኘት የሚቻል መሆኑን ሲያሳውቅ ስደተኛውም ሊመጠ ከሚችለው አደጋ እራሱን ይታደግ ዘንድ የሚቀጥሉትን ነጥቦች በስራ ላይ እንዲያውል ያሳስባል።
-የካሪታስ ቢሮ ከ አረብ 28-06 2013 ጀምሮ ዝግ ነው
-የ UNHCR የስደተኖች ቢሮ -ከ30-06- 2013 ጀምሮ ዝግ ነው
-የ አሚራ ቢሮ ከ 30-06-2013 ጀምሮ ዝግ ነው
-ሴንት አንደሮ ከ 30-06 2013 ጀምሮ ዝግ ነው
-ተዳሙን ቢሮ 30-06-2013 ጀምሮ ዝግ ነው
ከዚህም በመነሳት ማንኛውም ኢትዩጲያዊ ስደተኛ፦
- ከ 28-06-2013 ጀምሮ የግድ ካልሆነ በስተቀር ከቤት ባይወጣ ይመከራል
- ከቤት መውጣት የግድ በሚሆንበት ጊዜ ከሀገሪቱ ዜጎች ጋር የሚያመሳስል
አልባሳት መጠቀም
- ይህ ችግር እልባት እስኪያገኝ ድረስ ስደተኛው የተለያዩ ዝግጅቶች ካሉት ወደሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ይመከራል
- ስደተኛው በሚኖርበት አካባቢ ካሉት ሰዎች ጋርም ይሁን ከቤት አከራዩች ጋር ችግር ያለበት ከሆነ ለጊዜው ወደሌላ ሰፈር በመቀየር ይህን ክፉ ጊዜ እዲአሳልፍ ይመከራል
- የ ሀገሪቱ ዜጎች በሚያደርጉት አካባቢን የመተበቅ ስራላይ በጥንቃቄ መሳተፍ
- የግድ መንቀሳቀስ ያለብተ ስደተኛ የ UN ካርድ መያዝ አለበት
- በስራ ቦታ ያሉ ስደተኞች እዚያ ያለው ሁኔታ አሰጊ እሰካልሆነ ድረስ እረፍት ባይወጡ ይመከራል
- የውሀ የምግብ የመድሀኒት የመብራት የስልክና የ ኢነተርኔት ችግር ሊኖር ስለሚችል ለ-15 ቀን ያላነሰ አሰቤዛ ገዝቶ መጠበቅ የሰፈልጋለ
- ልጆች ላላችው እነዲሁ አሰፈላጊው ዝግጅተ እንዲያረጉ ይመክራል
ማሳሰቢያ—የጦር ሃይሉ ባወጣው መግለጫ መሰረት ማንናውም የውጭ ዜጋ እሁድ በ-30-06-2013 ከቤት መውጣት የለበትም።

Thursday, June 27, 2013

Norway could lose over 11,000 jobs in trade agreement

If the EU and the U.S. agree on a free trade agreement, Norway may lose more than 11,000 jobs, according to a German report.

If the EU and the U.S. agree on a free trade agreement, Norway may lose more than 11,000 jobs, according to a German report.
 The effects of Norway can be large  in economic and foreign policy. U.S. and EU are our main allies, but we are also outside when this agreement now being negotiated, says Ulf Sverdrup, director of the Norwegian Institute of International Affairs (NUPI), to the newspaper Aftenposten. In a recent report prepared by the German research institute Ifo on behalf of the Bertelsmann Foundation shows that Norway could lose about 11,500 jobs if there is agreement between the EU and the U.S. on a profound liberalization of trade. According to the report, unemployment here at home could increase by 0.44 percentage points. Today the unemployment rate of 3.5 percent.
 Ten days ago announced the leaders of the U.S. and EU that it will finally begin to negotiate a free trade agreement, which is several times previously been discussions about putting in the time. Earlier this week NHO made it clear that the government must work for the EFTA, which Norway is a part of, initiate parallel negotiations with the United States. - A free trade agreement between the U.S. and the EU have long been discussed, but it is the first time they actually sit down and begin to negotiate. The challenges are many, but the will and aspirations are big on both sides, says Sverdrup.


postd by Girum K.



በገዋኔ በፌደራል ፖሊስና በህዝቡ መካከል በተፈጠረ ግጭት ሰዎች ተጎዱ

576820_643438789017118_1777115518_n
ሰኔ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና :-ዛሬ ሰኔ 20፣ 2001 ዓም አንድ የአፋር ወጣት በኢሳዎች መገደሉን ተከትሎ የከተማዋ ነዋሪዎች ሬሳውን በመያዝ ተቃውሞአቸውን ለመግለጽ ፖሊሶች ወደ ሚገኙበት ካፕም ሲያመሩ የፌደራል ፖሊሶች ” ዘወር በሉ” በማለት ሰልፈኞችን ሲጠይቁ፣ ሰልፈኞችም ” ጥያቄያችን ሳይመለስ አንሄድም” በማለታቸው ተኩስ እንደተከፈተባቸው እና ሁለት ሰዎች እንደቆሰለባቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል። የሞቱ ሰዎች እንዳሉ የተጠየቁት የአካባቢው ነዋሪዎች ፖሊሶች ሊያስጠጉን ስላልቻሉ ለማወቅ አልቻልም የሚል መልስ ሰጥተዋል። ከቆሰሉት መካከል አንዱ ሆዱን ሌላው ጭንቅላቱን መመታታቸው ተናግረዋል።
የፌደራል ፖሊስ አባላት በአካባቢው የመሳሪያ ፍተሻ እናደርጋለን በማለታቸው ከወረዳው ፖሊሶች ጋር መጋጨታቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
በገዋኔ አካባቢ በአፋር እና በፌደራል ፖሊሶች መካከል የሚታየውን ተደጋጋሚ ግጭት በተመለከተ የአካባቢውን ባለስልጣናት ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
posted by Girum K