Saturday, August 31, 2013

የሰማይዊ ፓርቲ አመራሮች በስብሰባ ላይ እንዳሉ የወያኔ ፌደራል ፖሊስ ቢሮውን በመክበብ ሁሉንም የአመራር አባላትን በመኪና ጭኖ ወደ እስር ወስደዋቸዋል።


ከምሽቱ 1:00 ላይ የሰማይዊ ፓርቲ አመራሮች አራት ኪሎ 

አካባቢ በሚገኘው ጽ/ቤታቸው በስብሰባ ላይ እንዳሉ የወያኔ 

ፌደራል ፖሊስ ቢሮውን በመክበብ ሊቀ-መንበሩን ጨምሮ 

ሁሉንም የአመራር አባላትን በመኪና ጭኖ ወደ እስር 

ወስደዋቸዋል።በውጭም በውስጥም የሚኖረው መላው 

የኢትዮጵያ ህዝብ ድርጊቱን እንዲያወግዝና ለአለም-አቀፍ 

ተቁማትም ሁኔታውን እንዲያሳውቅ ጥሪ ቀርቧል። ሞት ለወያኔ 

ትግሉ ይቀጥላል።
                   
                  የሰማያዊ ፓርቲ መግለጫ፤

ትግላችን የህግ የበላይነትን ወደ ማስከበር ተሸጋግሯል!

ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ባካሄደው ታላቅ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለመንግሥት 

ያቀረብናቸው ጥያቄዎች መልስ ባለማግኘታቸው ለሕዝብ ቃል በገባነው መሠረት በድጋሚ ተቃውሞ ሰልፍ አቅዶ 

አስፈላጊውንእንቅስቃሴ እያደረገ ነው፡፡ ለዚህም ሥራ መሳካት ለሚመለከተው የመንግሥት አካል ነሐሴ 13 ቀን

2005ዓ.ም. በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን፣ መጀመሪያ ባቀረብነው ደብዳቤ ላይ ያልተካተቱ ጉዳዮችን
እንድናካትት ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ.ም. በተፃፈልን ደብዳቤ ተጠይቀን አስፈላጊውን መልስ አሟልተን ነሐሴ 17 

ቀን 2005 ዓ.ም. በተፃፈ ደብዳቤ አሳውቀናል፡፡

በአዋጁ በግልፅ እንደተደነገገው ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ህገ መንግሥታዊ መብት እንደሆነና ማንም ሊከለክለን 

እንደማይችል በማያሻማ መንገድ ተገልጿል፡፡ ሰልፉን የማሳወቁ ዓላማ የጥበቃ አገልግሎትና አንዳንድ አስተዳደራዊ 

ድጋፎችን ለማግኘት ነው፡፡ በዚህ አሰራር ውስጥ መንግሥት የጥበቃና የቦታ ችግር ካለ ሰልፉን ለሌላ ጊዜና ቦታ 

እንዲያደርግ ለሚመለከተው አካል ደብዳቤ በደረሰው በ24 ሰዓት ውስጥ በፅሑፍ መልስይሰጣል የሚል ድንጋጌ 

አለ፡፡ ነገር ግን በመንግሥትበኩል ላቀረብነው የመብት ጥያቄ ምላሽ መሰጠት ሲገባው እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ 

የመንግሥት መዋቅር ሙሉ በሙሉ በመጠቀምና ዜጐችን አስገድዶ ሰልፍ እንዲወጡ በማስፈረም ሰማያዊ ፓርቲ 

ሰልፍ በጠራበት ቀንና ቦታ ሌላ ሰልፍ በተደራቢ በሃይማኖት መቻቻል ስም ህገ መንግሥቱን በመጣስ የሃይማኖት 

ተቋማትን ለራሱ የድርጅት ፖለቲካ መጠቀሚያና የሰማያዊ ፓርቲን ህጋዊ እንቅስቃሴ ለመግታት እየተጠቀመበት 

ነው፡፡

በረከት ስምኦን በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ እየዶለቱ ነው – (ከኢየሩሳሌም አርአያ)


አቶ በረከት
በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ሊቀመንበርንት ከሚመራው ግንቦት ሰባት ጋር በተያያዘ በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ በረከት ስምኦን የሚመሩት የመንግስት አካል በምስጢር እየዶለተ መሆኑን ምንጮች ጠቆሙ። በቅርቡ በአንድ ድረገፅ ላይ የወጣውን የዶ/ር ብርሃኑን ንግግር በማስረጃነት ይዘው እየተንቀሳቀሱ ያሉት አቶ በረከትና ተከታዮቻቸው በአገር ውስጥ እየተንቀሳቅሰ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ « ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አለው፤ ከግንቦት ሰባት የገንዘብ ድጋፍ ይደረግለታል» በሚል እነበረከት ድምዳሜ ላይ መድረሳቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ የፓርቲውን አመራሮች «ከሽብረተኛ ቡድን ጋር በመገናኘት» ብለው ለመክሰስ ሴራ እያበጃጁ መሆኑን አስውታውቀዋል። የፓርቲው አመራሮችን ከማሰር ባለፈ «ሰማያዊ ፓርቲ በሽብርተኛ ድርጅት የሚረዳ ነው» በሚል በአገር ውስጥ የሚኖረውን የፓርቲው ቀጣይ ህልውና ለማክሰም ጭምር እየዶለቱ መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል። ከበረከት በተጨማሪ ደብረፂዮን ይህንን ሴራ በበላይነት እየመከሩበት እንደሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አሜሪካ ለሚገኝ አንድ ጋዜጠኛ ከገዢው ባለስልጣናት ዳጎስ ያለ ገንዘብ እንደተላከለት የቅርብ ምንጮች አጋለጡ። መጀመሪያ 250.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) ፣ በማስከተል 50.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) ሃዋላ እንደተደረገለትና ባጠቃላይ 300.00 (ሶስት መቶ ሺህ ብር) በዶላር ተመንዝሮ በእጁ እንደደረሰው ምንጮቹ ጠቁመዋል። ገንዘቡ ከነበረከት በኩል በምስጢር የተላከ መሆኑን ያጋለጡት ምንጮቹ በዚሁ መሰረት ጋዜጠኛው ለሕወሐት/ኢህአዴግ ማገልገል መቀጠሉንና በተለይ አሁን በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ እየተሸረበ ያለው ሴራ መነሻው ይህ ሰው እንደሆነ አያይዘው ገልፀዋል።

መንግስት ዘንድ ከፍተኛ መደናገጥ ተፈጥሯል!


ለዛሬ ታቅደው የነበሩ ግዙፍ የቅስቀሳ መድረኮች ተሰርዘዋል!
የሃይማቶች ጉባኤ ያዘጋጀው ነው ተብሎ በሚዲያ የተገለጸው የነገው ሰልፍ ሙስሊሙ ህብረተሰብ በነቂስ እንደሚሳተፍበት ካሳወቀ በኋላ እጣ ፈንታው ምን እንደሆነ ማወቅ አልተቻለም፡፡ ይህ ከፍተኛ ዝግጅት እና ወጪ ተደረጎለት የሰነበተውን ሰላማዊ ሰልፍ ድንገት ሙስሊሙ ህብረተሰብ በስፋት እንደሚገኝበት መታወቁን ተከትሎ በመንግስት ወገን አካባቢ ከፍተኛ ድንጋጤ በመፍጠሩ የሰልፉ እጣ ፈንታ አልተለየም፡፡ ትናንት አመሻሹ ላይ ሊካሄዱ ታስበው የነበሩ የሰልፍ ዝግጅት ግምገማዎች በዚሁ ምክንያት ሙሉበሙሉ መሰረዛቸው የታወቀ ሲሆን በወረዳና በክፍለ ከተማ አካባቢ ያሉ የመንግሰት ሀላፊዎችም ለከፍተኛ ጭንቀት ተዳርገዋል፡፡
‹‹አክራሪነትን ለማውገዝ›› በሚል መሪ አላማ በተዘጋጀው ሰልፍ መንግስት አዘጋጅ እንዳልሆ ሲገልጽ መሰንበቱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም የሰልፉን አጠቃላይ ዝግጅት ከአጀንዳ መረጣ ጀምሮ በፋይናንስ እና በቅድመ ዝግጅት በኩል እንዲሁም ከፍተኛ ሚዲያ ሽፋን በመስጠት ዝግጅቱን ሲመራ ቆይቷል፡፡ በክፍለ ከተማ እና ወረዳ ደረጃ ያሉ የመንግስተ ሀላፊዎችና ቢሮዎች በዚሁ ሰልፍ ላይ ሙሉ ጊዜያቸውን ሰጥተው የከረሙ ሲሆን በመንግስት ስር የተደራጁ የጥቃቅን እና አነስተኛ፣ የሴቶችና ወጣት ሊጎች፣ የኮብልስቶን ሰልጣኞችና የመንግስት ሰራተኞች እንዲሁም ሌሎችም በሰለፉ እንዲሳተፉና ቅስቀሳ እንዲደርጉ ሲደረግ ሰንብቷል፡፡
ሙስሊሙ ህብረተሰብ አክራሪነትን እንደሚያወግዝና እንደማይቀበል ለሁለት ዓመት በቆየው ሰላማዊ እንቅስቃሴው ደጋግሞ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡ ኮሚቴዎቻችን ሕገ መንግስቱ ቢፈቅድ አንኳ አክራሪነትንና ጽንፈኝነትን ፈጽመው እንደማይቀበሉ በተለያዩ መድረኮች ላይ ተናግረዋል፡፡ በተቃራኒው መንግስት መብት የጠየቀውንና አክራሪነትን የሚቃወመውን ሙስሊም ህብረተሰብ በአክራነት በመወንጀል ለመብት ጥያቄው ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ቆይቷል፡፡ መንግስት በእምነቶች መካከል መቃቃር እንዲፈጠር በማሰብ ሲነዛ የቆየውን ፕሮፖጋንዳ ሃለፊነት በጎደለው መልኩ በመንግስት ሚዲያዎች ሲያሰራጭም ሰንብቷል፡፡
በክልልሎች በግዳጅ ህብረተሰቡን ወደ ጎዳና በማስወጣት ያካሄዳቸውን ሰልፎች ተከትሎ በአዲስ አበባ ደረጃ አክራሪነትን በመቃወም ስም ሙስሊሙን የሚያወግዝና መብት ጠያቂውን ህብረተሰብ በተራ የፖለቲካ ስሌት ለማንጣጣት የሚጥር መድረክ ቢጠራም ሙስሊሙ ሁሉንም አይነት አክራሪነት በመቃወም ጭምር ሰልፉ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡ የሙስሊሙ ህብረተሰብ በሰልፉ በስፋት መገኘት ውሳኔ ስጋት ያሳደረበት መንግስት ከፍተኛ ድንጋጤ እና መረበሽ ውስጥ ገብቷል፡፡ በዚህም ምክንያት ለዛሬ በከተማዋ ሊካሄዱ ታስበው ነበሩ ግዙፍ ቅስቀሳዎች ተሰርዘዋል፡፡ በመኪናዎችና በግዙፍ ሜጋ ስፒከሮች በከተማዋ ሊካሄዱ ታስበው የነበሩ የዛሬ ዋና ዋና ቅስቀሳዎች ከላይ በወረደ ትእዛዝ ምክንያት ከመሰረዛቸውም በላይ ለሰልፉ ተሳታፊዎች ይዘጋጃሉ የተባሉ የሕዝብ ማመላለሻ ነጻ ተሸከርካሪዎችም እንደማይኖሩ ተነግሯል፡፡ ሙስሊሙ ህብረተሰብ ነገ በሚደረገው ሰልፍ በስፋት ነቅሎ በመውጣት ፍጹም ዲሲፕሊን በታከለበት መልኩ አክራሪነትን እንደሚያወግዝ ይጠበቃል፡፡ ለዚህም ከፍተኛ የቅስቀሳ ስራዎች በመሰራት ላይ ናቸው፡፡
ድምፃችን ይሰማ

በሁለት ሰልፎች ምክንያት ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂው መንግሥት ነው ብሏል፡፡

ማሳወቅ ባለብን ሰዓት አሳውቀናል፤ ለሚፈጠረው ችግር መንግስት ሀላፊነቱን ይወስዳል- ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
ሰማያዊ ፓርቲ ሳያስፈቅድ በሚያካሂደው ሰልፍ ለሚፈጠር ችግር ሀላፊነት ይወስዳል- አቶ ሽመልስ ከማል
የሰማያዊ ፓርቲ የነገው ሰልፍ ህገወጥ ነው - ም/ኮሚሽነር ግርማ ካሳ
በነገው እለት ሰማያዊ ፓርቲና የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ የጠሩ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ፅ/ቤት፤ የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ህገወጥ ነው ብሏል
ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የሚመለከተውን አካል አሳውቄአለሁ ያለው ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ፤ ከሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በፊት ማሳወቁን ገልፆ፤ በሁለት ሰልፎች ምክንያት ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂው መንግሥት ነው ብሏል፡፡
“ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፉ አልተፈቀደለትም ያሉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል፤ ፓርቲው ይህንን ተላልፎ በሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ለሚፈጠር ማንኛውም ችግር ሀላፊነቱን ይወስዳል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የሚፈልግ አካል ሰልፉን ያደራጀውን ሰው፣የሰልፉን አላማ ይዘት፣ የሚወጣውን የሰው መጠን ግምት፣የሚካሄድበትን ጊዜና ቦታ መግለፅ እንዳለበት የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህን ማሳወቅ ብቻ ሳይሆን ማስፈቀድም እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት ተናግረዋል፡፡ “ማሳወቅ ማለት ማስፈቀድ አይደለም” ያሉት አቶ ሽመልስ፤ ካሳወቁም በኋላ ፍቃድ መጠየቅ የግድ ነው ብለዋል፡፡ “በበኩሌ የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ፅህፈት ቤት እሁድ የአክራሪነትና የፅንፈኝነት እንቅስቃሴን በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማስፈቀዱን አውቃለሁ” ያሉት አቶ ሽመልስ፤ በየትኛውም አገር በአንድ ቀንና በአንድ ቦታ ሁለት ሰላማዊ ሰልፎች ማካሄድ ስለማይፈቀድ፣ ፈቃድ ሰጭው አካል ይህን እያወቀ ለሰማያዊ ፓርቲ ፈቃድ ይሰጣል የሚል እምነት የለኝም ብለዋል፡፡ “በመሆኑም ሰልፉን የሚያካሂደው የተፈቀደለት አካል ነው” ብለዋል፡፡ አቶ ሽመልስ አክለውም፤ “በየትኛውም አገር ፍቃድ ሳይገኝ ሰላማዊ ሰልፍ አይወጣም፣ማሳወቅ ብቻ በቂ ነው ብሎ ህግን በመናቅ የትም አይደረስም፣ይህን ተላልፎ ቢገኝ ለሚፈጠረው ችግር ፓርቲው ሀላፊነት እንደሚወስድ ራሱም ያውቀዋል” ብለዋል፡፡ “በአንድ ቀን ሁለት ሰላማዊ ሰልፎች የማይፈቀዱት የተለያዩ ግጭቶች እንዳይፈጠሩ፣ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠርና የፀጥታ ሀይሎች ወደተለያዩ ስራዎች ሊሰማሩ ስለሚችሉ የፀጥታ ችግር እንዳይከሰት ነው” ሲሉ አቶ ሽመልስ ገልፀዋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው ከሶስት ወር በፊት በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ያነሳቸው የህዝብ ጥያቄዎች ካልተመለሱ፣ ከሶስት ወር በኋላ ሁለተኛውን ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚጠራ በተደጋጋሚ መግለፃቸውን አስታውሰው፤ ይህም ጊዜ ነገ መሆኑንና አስፈላጊውን መስፈርት ማሟላታቸውን ተናግረዋል፡፡ “እኛ የማሳወቂያ ደብዳቤውን ያስገባነው ከሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ፅ/ቤት በፊት ነው” ያሉት ኢ/ር ይልቃል፤ መንግስት በእኛ ላይ የተደረበውን ሰላማዊ ሰልፍ መሰረዝ እንዳለበት በመግለጫ ማሳወቃቸውንና ሰልፉን ከማካሄድ የሚገታቸው እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ “ሁለት ሰላማዊ ሰልፎች ሲካሄዱ ለሚፈጠረው ችግር መንግስት ሀላፊነቱን ይወስዳል” ሲሉም አሳስበዋል፡፡
ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ፅ/ቤት የማሳወቂያ ደብዳቤውን ካስገቡ በኋላ ፅ/ቤቱ የስብሰባውን አላማ፣የትና መቼ እንደሚያካሂዱ፣የሰው ብዛት ምን ያህል እንደሚገመት ፓርቲው እንዲያሳውቀው በደብዳቤ በጠየቀው መሰረት ለጥያቄዎቹ ሁሉ በደብዳቤ ምላሽ መስጠታቸውን ኢ/ር ይልቃል አስታውሰው፤ ነገር ግን ማሳወቂያ ፅ/ቤቱ በ48 ሰዓት ውስጥ ምላሽ ባለመስጠቱ እንደተፈቀደ ቆጥረን ዝግጅታችንን አጠናቀናል ብለዋል፡፡ በመሆኑም ከሰማያዊ ፓርቲ በኋላ መጥቶ ሰልፍ የሚያካሂደውን አካል በማስቆም፣ መንግስት ሀላፊነቱን መወጣት አለበት ብለዋል - የፓርቲው ሊቀመንበር፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ማርቆስ ብዙነህ፤ “እኔ የማውቀው አንድ ሰላማዊ ሰልፍ ነው፤ የሰማያዊ ፓርቲ ህገወጥ ነው” በማለት መልሰዋል፡፡ ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ በዕለቱ ስለመካሄዱ ለፓርቲው አሳውቀው እንደሆነ የተጠየቁት አቶ ማርቆስ፤ “ደብዳቤ ፅፈን ስንሰጣቸው የፓርቲው ሰዎች አንቀበልም በሚል ወርውረውት ሄደዋል” ብለዋል፡፡ ጉዳዩን አስመልክተን የጠየቅናቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል፤ “ፅ/ቤቱ በቃልም በደብዳቤም ያሳወቀን ነገር የለም፤ እኛም በነገው ዕለት ሰልፉን እናካሂዳለን” በማለት የፅ/ቤቱን ምላሽ አጣጥለውታል፡፡ ትናንትና ረፋድ ላይ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጠርቶ እንዳነጋገራቸው የገለፁት ኢ/ር ይልቃል፤ “ሰላማዊ ሰልፍ እንደምታካሂዱ የደረሰን መረጃ የለም” መባላቸውን ጠቁመው፤ ማሟላት ያለባቸውን መስፈርት እንዳሟሉ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ግርማ ካሳ አሳውቀው መውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ በስልክ ያነጋገርናቸው ም/ኮሚሽነር ግርማ ካሳ፤ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሂድ ከሚመለከተው አካል ደብዳቤ እንዳልደረሳቸው ገልፀው፣ ሰማያዊ ፓርቲም ሰልፉ የተፈቀደበትን ማስረጃ ማቅረብ እንዳልቻለ ተናግረዋል፡፡ “በመሆኑም የነገው የሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ህገ ወጥ ነው” ሲሉ አረጋግጠዋል፡፡

ሰላማዊ ሰልፉ ያለፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል- ፖሊስ


በሃይማኖት ሽፋን የሚደረገውን የአክራሪነት እንቅስቃሴ ለመቃወም የአዲስ አበባ ከተማ የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ጉባኤ ነገ ነሃሴ 26 የጠራው የሰላማዊ ሰልፍ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለማድረግ መዘጋጀቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፉ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅም የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮማንድ ፖስት አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቋል ብለዋል፡፡

ሰልፉን ለማካሄድ እውቅና ያገኘው የከተማዋ የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ጉባዔ ብቻ ነው ያሉት ምክትል ኮሚሽነሩ ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንዳላገኘና በእለቱም ፓርቲው ሰልፉን ማካሄድ እንደማይችል ገልፀዋል፡፡

በፓርቲው ስም ሰልፍ ለማካሄድ ከተሞከረ ፖሊስ ሰልፉን እንደሚያስቆምና ህጉን ተላልፈው ሰልፉን ባካሄዱት ላይም ፖሊስ እርምጃ እንደሚወስድ ተናግረዋል፡፡

ለሰላማዊ ሰልፉ ሲባልም ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ ሰልፉ እስኪጠናቀቅ ድረስ ወደ መስቀል አደባባይ የሚያስገቡ መንገዶች ዝግ ይሆናሉ ብለዋል፡፡

ዝግ የሚሆኑትም መንገዶች ከኡራዔል ወደ ባንቢስ እና መስቀል አደባባይ፤ ከቤተ መንግስት ወደ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን እና መስቀል አደባባይ፤ ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሃር እና መስቀል አደባባይ፤ ከቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባይ፤ ከተክለሃይማኖት ሰንጋ ተራ ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱት መንገዶች ናቸው፡፡

ህብረተሰቡም ይህንን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያካሂድ እውቅና ከተሰጠው የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ጉባዔ ውጭ በእለቱ ሰልፍም ሆነ ስብሰባ እንዲያደርግ እውቅና ያገኘ የፖለቲካ ፓርቲ የሌለ መሆኑን ተገንዝቦ ከፀጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ኮሚሽኑ ጠይቋል፡፡


ሪፖርተር፤ አበበ ባዩ

Friday, August 30, 2013

የአጽዋማት ሥርዐት......ሊቀ ሥዩማን ራደ አስረስ

ክፍል አንድ

አጽዋማት፡- ጾም ለተወሰነ ሰዓት ከሁሉም ምግብ መከልከል ሁሉንም ምግብ መተው ነው፣ ለተወሰኑ ቀናት ማለት የጾሙ ቀናት እስኪያልፍ ድረስ ከተወሰኑ ምግቦች መከልከል የተወሰኑ ምግቦችን መተው ነው፣ ይኸውም ጥሉላትን ፈጽሞ መተው ሰውነትን ከመብልና ከመጠጥ መከልከል መጠበቅ ነው፡፡ ጾም ከጥሉላት መከልከል ብቻ ሳይሆን የሰው ልጆችን ከሚጐዳ ነገር ሁሉ መከልከልንና ለሌሎች መልካም ሥራ መሥራትንም ይጨምራል፡፡
በማንኛውም የሃይማኖት ሥርዓት ጾም አለ፤ የአፈጻጸሙ ሥርዓት ግን የተለያየ ሁኖ ይታያል፤ ለምሳሌ ያህልም ዕብራውያን ሲጾሙ ውለው ማታ ጥሉላት ይመገባሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ የክርስትናው እምነት ተከታይ እንደእኛይቱ ቤተ ክርስቲያን ሲጾሙ ውለው ሰዓት ሲደርስ እህልና ውሃ ብቻ ይቀምሳሉ እንጂ የጾሙ ወር ወይም ሳምንት እስኪፈጸም ድረስ ጥሉላት ፈጽሞ ክልክል ነው፤ የአጽዋማት ሥርዓት ሲባል ጾም እንዴት እንደሚገባና እንዴት እንደሚወጣ፣ እንዴትና ለምን እንደሚጾም ለይቶ ማወቅና እንደ ሥርዓቱ መፈጸምን የሚያመለክት ነው፤ የጾምን አላማና ጥቅም በሚመለከት የሸዋ ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ" በሚለው መጽሐፋቸው "የበዓላትና የአጽዋማት ቀኖና" በሚል ርእስ እንደሚከተለው ገልጠውታል፡፡ "ጾም /ጦም/ ማለት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል መወሰን ማለት ነው፡፡ ወይም ለሰውነት የሚያምረውንና የሚያስጐመዥውን ነገር መተው ማለት ነው፡፡ ጾም ከሃይማኖት ጋር ዘለዓለማዊ ዝምድና ስላለው ሃይማኖት ባለበት ቦታ ሁሉ ጾም አለ፡፡ ይልቁንም በብሉይ ኪዳን ጾም ከፍተኛ ቦታ አለው፡፡ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ከእግዚአብሔር ጋር በሚገናኙበት ወራት እህልና ውሃ በአፋቸው አይገባም ነበር፡፡ /ዘፀ፡34፡28/ በኀጢአት ብዛት የታዘዘው የእግዚአብሔር መዓት የሚመለሰው ሕዝቡ በጾም ሲለምኑትና ሲማልዱት ነበር፡፡ /ዮናስ 2፣7-10/ "በሐዲስ ኪዳንም ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ ሳይሆን ራሱ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሥራ መጀመሪያ አድርጎ የሠራው ሕግ ነው፡፡(ማቴ 4፣2፤ ሉቃ.4፣2) ይህም ብቻ ሳይሆን በቁራኝነት አብሮ የሚኖር መንፈስ ርኩስ ሰይጣን እንኳ በጾም የሚወገድ መሆኑን መድኀኒታችን ተናግሮአል፡፡ (ማቴ.17፣21፤ ማር.9፣2) ቤተ ክርስቲያንን እንዲያገለግሉ የታዘዙ ሐዋርያትም በየጊዜው ከመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ የሚቀበሉት በጾምና በጸሎት ላይ እንዳሉ ነበር፡፡ (የሐ.ሥራ 13፣2) ለስብከተ ወንጌል የሚያገለግሉ ዲያቆናትና ቀሳውስትም የሚሾሙት በጾምና በጸሎት ነበር፡፡ (የሐ.ሥራ 13፣3፤ 4፣23፤) እነቆርኔሌዎስ ያላሰቡትን ያዩና ያገኙ በጾምና በጸሎት ፈጣሪያቸውን ማልደው ነው፡፡ (የሐ.ሥራ 10፣30) "የጾም ሃይማኖታዊ ትርጒም ፈጣሪን መለመኛ ከኀጢአት ቊራኛ መላቀቂያ መሣሪያ ስለሆነ በጾም ወራት ላምሮት ለቅንጦት የሚበሉ ወይም ለመንፈሳዊ ኀይል ተቃራኒ የሆነ ሥጋዊ ፍትወትን የሚያበረታቱ የአልኮል መጠጦችን፣ ሥጋንና ቅቤን፣ ወተትንና እንቁላልን ማራቅ ታዟል፡፡ ከመባልዕትና ከሌላው ደስታ ሁሉ ጋር ባልና ሚስት በምንጣፍ በአልጋ አይገናኙም፡፡ (1ቆሮ.7፣5) ጾም በትምህርተ ሐዋርያትና በሊቃውንትም ዘንድ ሲሰበክ ኑሯል፡፡ ነዳያንን ለመመገብ የሚጾም ንዑድ ነው፤ ክቡር ነው፡፡ እንደተባለ ጦመኛው ለምሳው ወይም ለራቱ ያለውን ወጭ ነዳያን እንዲረዱበት ለድኩማን መርጃ ድርጅት ወይም በቤተ ክርስቲያን አካባቢ ለሚገኙ ነዳያን መስጠት ጾሙን የበለጠ ክርስቲያናዊ ያደርገዋል፡፡ "ጾም የታሪክ ድርጊቶችን እያስታወሱ ከኀጢአት ለመንጻት ስለራሱ የታሰበውን ለነዳያን በመስጠት የሚጾም መሆኑን ተረድተናል፡፡ ጾም ለራስ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም፤ ለወዳጅ ብቻ ሳይሆን ለጠላትም ይጾማል፤ ‹ለሚያሳድዱህ ጹምላቸው› እንደተባለ (ዲድ፡1፣3፤) በደዌ ዳኛ በአልጋ ቊራኛ የተያዙትን፣ በምርኮና በስደት ያሉትንም በጾም ወራት ማስታወስና መጸለይ ይገባል፡፡ በጾም ወራት ከመባልዕት መከልከል ብቻ ሳይሆን ዐይን ክፉ ከማየት፣ አንደበት ክፉ ከመናገር፣ ጆሮ ክፉ ከመስማት መቆጠብ እንደሚገባ ተጽፎአል፡፡ "ይጹም ዐይን፣ ይጹም ልሳን፣ እዝንኒ ይጹም እምሰሚዐ ኀሡም በተፋቅሮ" (ቅዱስ ያሬድ ድጓ) በሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ባህልና ትውፊት ውስጥ ያሉ የምዕራብም ሆኑ የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ከሐዋርያት የወረሱት የጾም ሕግና ሥርዐት አላቸው፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ከመጀመሪያዎቹ አብያተ ክርስቲያናት አንድዋ ስለሆነች ይህ የጾም ሕግና ሥርዓት አላት፡፡ በሕጓም መሠረት ሰባት የጾም ወራት አሏት፡፡ እነርሱም፡-
1. ዐቢይ ጾም፣
2. ጾመ ሐዋርያት፣
3. ጾመ ፍልሰታ፣
4. ጾመ ነቢያት፣
5. ጾመ ገሃድ፣
6. ጾመ ነነዌ፣
7. ጾመ ድህነት ናቸው፡፡

ክፍል ሁለት


በብሔርተኝነት ስም ታሪክንና የኢትዮጵዊነትን መንፈስ ማጣጣል ተቀባይነት የለውም

August 29, 2013

በፍቅር ለይኩን
በአንድ ወቅት በደቡብ አፍሪካዊቷ ከተማ በኬፕታውን የሚኖር አንድ በንግድ ሥራ የሚተዳደር  ኢትዮጵያዊ ጎልማሳ አንድ አሳዛኝ ገጠመኙን እንዲህ አጫውቶኝ ነበር፡፡ ይህን ታሪኩን ያካፈለኝ ኢትዮጵያዊ ጎልማሳ የሥራ ቦታው ላይ ከአንድ ከኦሮሞ ብሔር ተወላጅ ጋር በተነሳ ጠብ በተፈጠረ ግጭት የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ የሆነው ጓደኛውን አንድ የፊቱን ጥርሱን በቦክስ ያወልቀዋል፡፡ የጥርሱን መውለቅ የሰሙ የዚህ ሰው ጓደኞችም ተሰባስበው ይህን ሰው ካልገደልን በማለት ሲጋበዙ ነገሩ በሰላም ያልቅ ዘንድ አንዳንድ የሚያውቋቸው ሰዎች ለሽምግልና ጣልቃ ይገባሉ፡፡
በሽምግልና ድርድር ላይ እያሉም የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ የሆነው ጓደኛውን ጥርስ ያወለቀው ሰው የአያቱ ስም የኦሮሞ ስም ሆኖ ይገኛል፡፡ እነዛም በእንዴት ተደፍረን፣ ይህን ሰው ካልገደልን በማለት ሲዝቱ የነበሩ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆችም፣ ይኽ ሰው ለካ ወገናችን ነው በማለት ለበቀል ያነሱትን ሰይፋቸውን ወደ ሰገባው ይመልሳሉ፡፡ ሐሳባቸውን በመቀየር ጉዳዩ በሰላም ተቋጭቶ፣ በሃያ ሺሕ የደቡብ አፍሪካ ራንድ ካሳ ክፍያ እንዲጠናቀቅ ተስማምተው እርቅ ማውረዳቸውንና አያቴ ስም የኦሮሞ ስም በመሆኑ ከጉድ ወጣሁ ሲል በግርምት መንፈስ ሆኖ ገጠመኙን አጫወተኝ፡፡
ይህ ሰው እስከዛች ቀን ድረስ ስለ አያቱ ኦሮሞነትም ሆነ ስለመጣበት ብሔር ወይም ጎሳና ማንነት በቅጡ አስቦ ወይም ትዝ ብሎት እንደማያውቅና ይህ ገጠመኙ ግን ከሚኮራበት ከኢትዮጵያዊነት ማንነቱ ባሻገርም ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ ስለሰኟት ሕዝቦቿ ታሪክ፣ ባህል፣ ማንነትና ቅርስ ለማጥናት የማንቂያ ደወል ሆነኝ ሲል ነግሮኛል፡፡ በነገራችን ላይ ይህ ሰው በተለያዩ ጊዜያት ወደ ደቡብ አፍሪካ በስደት የገቡና ኖሮአቸውን በዛው ያደረጉ የኦሮሞ ተወላጆች ለደቡብ አፍሪካ መንግሥት የፖለቲካ ጥገኝነት ጥያቄ በሚያቀርቡበት ወቅት የተፈጠረውን እሰጥ አገባም እንዲህ ጨምሮ ተርኮልኛል፡፡
የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ ሆኑ ስደተኞች ለፖለቲካ ጥገኝነት ብቁ የሚያደርጋቸውን ቅፅ በሚሞሉበት አጋጣሚ አብዛኛው የኦሮሞ ተወላጆች ዜግነት ወይም አገር በሚለው ክፍት ቦታ ላይ ‹‹ኦሮሚያ›› በማለት በመሙላታቸው የደቡብ አፍሪካ ‹‹ሆም አፌር ቢሮ›› የሥራ ባልደረቦች እኛ ‹‹ኦሮሚያ›› የሚባል አገር አናውቅም በማለታቸው በተነሳ ክርክር፣ እነዚህ የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ የሆኑ የፖለቲካ ጥገኝነት ፈላጊዎች፣ ‹‹ኦሮሚያ በቀድሞዋ አቢሲኒያ በአሁኗ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ስር ምትማቅቅ አገር ናት፡፡›› በማለት በማስረዳት ዜግነት በሚለው ክፍት ቦታ ላይ ‹‹ኦሮሚያ›› የሚለው ማንነታቸው እንዲሞላላቸው ቢጠይቁም ተቀባይነት በማጣታቸው እየጎመዘዛቸው ቢሆንም የማያምኑበትን የኢትዮጵያዊ ዜግነት በክፍት ቦታው ላይ ይሞሉ እንደነበር ይህ ሰው ጨምሮ ነግሮኛል፡፡

ይህንና ይህን የመሳሰሉ ብሔርን ማእከል ያደረጉ አሳዛኝ ገጠመኞች በኢትዮጵያም ሆነ በውጭ አገር ተደጋግመው የሚከሰቱ መሆናቸው ደጋግምን ያየነውና የሰማነው እውነታ ነው፡፡ በአውሮፓ፣ በአሜሪካ፣ በአውስትራሊያና በደቡብ አፍሪካ ዛሬ ዛሬ በትግሬ፣ በአማራ፣ በኦሮሞ … ወዘተ ስምና ማንነት የራሳቸውን ወሰን ወስነውና አጥር ከልልው የሚኖሩና ይህና ያ ብሔር በእኔና በዚህ ብሔር ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው በደል፣ ግፍና ጭቆና አድርሶብናል በሚል የየራሳቸውን የጭቆና ታሪክና የተጋድሎ ገድል ጽፈውና አጽፈው ያሉ፣ ከዚህም የተነሳ ደግሞ ለበቀል የሚፈላለጉና በጎሪጥ የሚተያዩ ሕዝቦች ኢትዮጵያ በምትባለው ምድር ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ነው፡፡
ይህን ከላይ በመግቢያችን የገለጽኩትን አሳዛኝ ገጠመኝ ወይም ታሪክ ለዚህ ጹሑፍ መግቢያ ይሆነኝ ዘንድ የመረጥኩት ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ስለ ኢትዮጵያዊነትና ኦሮሙማ (ኦሮሞ ናሽናሊዝም) በተመለከተ ‹‹በገዳ ዶት ኮም›› እና በሌሎች በተለያዩ ድረ ገጾች ሰፋ ያለ ውይይትና ክርክር ተደርጎ ነበር፡፡ በዚህ ከስምንት የማያንሱ ማእከላቸውን አውሮፓና አሜሪካ ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የኦሮሞ ምሁራን ባደረጉት ውይይትና ክርክር ከተሳተፉት ፖለቲከኞችና የኦሮሞ ምሁራን መካከል ዶ/ር በያን አሶቦና ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
ይኸው የኢትዮጵያዊነትና የኦሮሙማ ሙግትም የፓል ቶክ ዋና የመወያያ ርዕስ ሆኖ ነበር፡፡ ይህ ውይይትና ክርክር ገና ሳይበርድና ሳይቋጭ ነበር በዛው ሰሞን ወጣቱ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁርና ተንታኝ ጃዋር ሙሐመድ ከአልጄዚራ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ለዓመታት በዘለቀው የኦሮሞ ጥያቄ፣ የነፃነት ትግል ታሪክ ጉዳይ ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ የሰጠው፡፡ ጃዋር I am First Oromo. Ethiopia is imposed on me የሚለው አቋሙን ግልጽ ካደረገ በኋላ የኦሮሞን ታሪክና የኦሮሞን የዓመታት ጥያቄ በተመለከተ የፖለቲካ ተንታኙን የጃዋርን ትንታኔና አቋም በመቃወምም ይሁን በመደገፍ የተለያዩ ሐሳቦች መንሸራሸር ጀመሩ፣ አሁንም ድረስም እየተንሸራሸሩ ነው፡፡
ባለፉት ሰሞናትም በተለያዩ በይነ መረቦችና በማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይም የጃዋርን ሐሳብ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች በየበኩላቸው አቋማቸውን ለመግለጽ ሞክረዋል፡፡ አንዳንዶችም ስድብ ቀረሽ በሚመስል ጨዋነትና ቅንነት በጎደለው መንፈስ ጃዋር ባነሳው ሐሳብ ላይ የውይይት መድረኩን የሚያጠለሹና የሚበርዙ እሳቤዎችን ከስድብ፣ ከዛቻና ከማስፈራሪያ ጭምር ሲያዘንቡም ታዝበናል፡፡ ከዚህ ውጪ ደግሞ ሰብአዊ ፍቅር፣ ጨዋነትና ቅንነት በተሞላበት መንፈስ ከኦሮሞም ይሁን ከሌላ ብሔር ተወላጆች ዘንድ፣ ሚዛናዊ የሆነ፣ ከጭፍን ጥላቻና ከበቀል ስሜት በጸዳ መንፈስ  ሐሳባቸውንና አቋማቸው የገለጹም ጥቂት ጸሐፊዎችና ተንታኞችም ብቅ ብቅ ብለው ነበር፡፡
እኔም በዚሁ ሰሞነኛ በሆነው የኦሮሞ ሕዝብን ታሪክና ጥያቄ በተመለከተ ለኦሮሞ ሕዝብ ነፃነትና መብት ቆመናል በሚሉ አንዳንድ የኦሮሞ ምሁራንና ፖለቲከኞች ዘንድ በኦሮሙማ (በኦሮሞ ናሽናሊዝም)፣ በኢትዮጵያ ታሪክና በኢትዮጵያዊነት ላይ በሚያነሷቸው አንኳር ሐሳቦችና በሚያራመዱት አቋሞቻቸው ዙሪያ ላይ ጥቂት የመወያያ ሐሳቦችን ለማጫር ወደድኩ፡፡
በእርግጥ ይህ ለውይይት ማጫሪያ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ አጭር ጽሑፍ የኦሮሞ ተወላጅ ምሁራንና ፖለቲከኞችን፣ አሊያም ደግሞ በኦሮሞ ሕዝብ ስም ተቋቋመው እየተንቀሳቀሱ ያሉ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ታሪክና በኢትዮጵያዊነት ላይ ያላቸውን አቋማቸውንና ለኦሮሞ ሕዝብ አለን ስለሚሉት የትግል አቅጣጫዎቻቸውን ለመተንተን፣ ለመተቸትና ለመገምገም አይደለም አነሳሱ፡፡ ይህን ለማድረግ እንሞክር ቢባል እንኳን በእነዚህ ጥቂት ገጾች ለመሞከር የሚታሰብ አይሆንም፡፡
ለዚህም እንደ ዋና ሆነው ከሚነሱት ዐበይት ምክንያቶች መካከል ደግሞ በኦሮሞ ሕዝብ ስም እየተንቀሳቀሱ ያሉ በዓላማም በአቋምም የተለያዩ ፓርቲዎች መኖራቸው፡፡ እንዲሁም እነዚሁ ፓርቲዎችም የኦሮሞን ሕዝብን ታሪክና ጥያቄ  በተመለከተ የሚያራምዷቸው አቋሞችና ጥያቄዎች ‹‹ከባርነት ወይም ነፃነት›› ወይም ደግሞ ‹‹ከአቢሲኒያ/ከዛሬዋ ኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ነፃ የመውጣት ጥያቄ ነው፡፡›› ከሚለው ፖለቲካዊ አቋም አንስቶ በተለያዩ የኦሮሞ ተወላጅ ምሁራንና ፖለቲከኞች ዘንድ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች ባሉ የኦሮሞ ሕዝብ ታሪክ፣ ባህል፣ እምነትና ቅርስ አኳያ ያሉት አመለካከቶችና ትንታኔዎች መንገዳቸው የየቅል መሆኑን ነገርዬውን ቀላል አያደርገውም ብዬ ስለምገምት ነው፡፡
ለአብነትም ያህል የኦሮሞን ብሔርተኝነት በእጅጉ ያራምዱና ‹‹የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ የነጻነት ጥያቄ ነው፡፡›› ሲሉ የነበሩ አንዳንድ የኦሮሞ ምሁራንና ፖለቲከኞች በጊዜ ሂደት ኦሮሞ በኢትዮጵያ በቆዳ ስፋት ትልቁና የሕዝቡም ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ውስጥ ግዙፍ ሆነ ቦታ ሊሰጠው ይገባል፣ የኦሮሚፋም በኢትዮጵያ የፌዴራል መንግሥት ፖለቲካ አሥተዳደር ውስጥ የፌዴራል መንግሥቱ  ቋንቋ መሆን የሚችልበት መንገድ ሊታሰብብት ይገባዋል፣ የሚሉ የተለሳለሱ አቋሞችን የሚያራምዱ የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ ፖለቲከኞችም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብቅ ብቅ ማለታቸውንም ታዝበናል፡፡
ስለሆነም በዚህ ጽሑፍ የኦሮሞን ታሪክ፣ ባህል፣ ማንነት፣ የኦሮሞን የመብት ጥያቄና ትግል ተመለከተ በፊትም ሆነ በተለይም ደግሞ ከሰሞኑን የፖለቲካ ተንታኙ ጃዋር ሙሐመድ ባነሳው የኢትዮጵያዊነትና የኦሮሙማ አንኳር እሳቤዎች ላይ ተመርኩዤ ጥቂት ነገሮችን ለማለት ወደድኩ፡፡
እንደሚታወቀው ባለፉት ሁለት ዐሥርት ዓመታት ውስጥ የእከሌ ብሔር ወይም ጎሳ በዚህኛው ብሔር ወይም ጎሳ ላይ ለፈጸመው በደልና ጭቆና በሚል ያልተወራረዱና ጊዜ እየጠበቁ ቦግ እልም የሚሉ ምሬቶችን፣ ቁጣዎችንና የበቀል ሰይፎችን በተለያዩ የአገራችን ክልሎች መከሰታቸውን ታዝበናል፡፡ ይህን እኩይ የሆነ የበቀል ሒሳብ በማወራረድ የተጠመዱ አንዳንድ ፓርቲዎች፣ ፖለቲከኞችና ግለሰቦችም ሆን ብለውና ያልተገባ ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግበስበስ ሲባል እውነታን በማጣመም በሚጻፏቸውና በሚያጽፏቸው የተዛቡ የታሪክ ድርሳናትና ገድሎቻቸው፣ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ትናንትና ያልነበረ ዛሬም የሌለ ቅዠት ወይም ሕልም ነው እስኪባል ድረስ ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በርካታ ትንታኔዎቻቸውን ሰምተናል፣ የዳጎሱ ጥናታዊ ጽሑፎቻቸውንም አስነብበውናል፡፡
በዚህ እነዚሁ የብሔር ፖለቲካ ጽንፈኞች፣ በቀልን ሰባኪዎች፣ የብሔራዊ መግባባትና እርቅ ተቀዋሚዎች በተጻፉ የተዛቡ ታሪኮችና ያልተወራረዱ የበቀል ሒሳቦች ክፉ ስብከት የተነሣም ለዘመናት ተዋደውና ተከባብረው፣ በጋብቻና በአምቻ ተሳስረው፣ እኔ ትብስ አንተ ትብስ ብለው የኖሩ ሕዝቦች የተሳሰሩበትን የአንድነት ድርና ማግ ለመበጠስ ሲባል የተደረጉ አያሌ ዘመቻዎችንም በዘመናችን በሐዘንና በግርምት ሆነን አስተውለናል፡፡
ዛሬም ድረስ ለኦሮሞ ሕዝብ መፍትሔው የእኔ የፖለቲካ አቅጣጫ ነው የሚሉ በርካታ የኦሮሞ ምሁራን፣ ፖለቲከኞችና ፓርቲዎች በአገር ውስጥና በውጭ አገር ሆነው ለኦሮሞ ሕዝብ ይጠቅማል በሚሉት መንገድ የራሳቸውን አቋም በማራመድ ይጻፋሉ፣ ይወያያሉ፣ ይከራከራሉ፣ ይሟገታሉም፡፡
ይሁን እንጂ እስካሁኗ ቅጽበት ለኦሮሞ ሕዝብ ነፃነት፣ መብትና ጥቅም ቆመናል በሚሉት በበርካታ የኦሮሞ ፖለቲከኞች፣ ምሁራንንም ሆነ ፓርቲዎች ዘንድ ቢያንስ ባለፉት ሁለት ዐሥርተ ዓመታት የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክና ጥያቄ በማስተጋባትና በመፍትሔ አቅጣጫዎችም ዙሪያ በሚያራምዱት አቋማቸው እርስ በርሳቸው የተለያዩና የተከፋፈሉ መሆናቸውን በተለያዩ አጋጣሚዎች ዐይተናል፡፡ በዋነኝነት የኦሮሞ ሕዝብን ጥያቄ ለመፍታት ከእኔ ወዲያ ለአሳር በማለት ሲምል ሲገዘት የነበረው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) በዕድሜ የሚያክለውና የሚስተካከለው ባይኖርም ዛሬም ድረስ በተለያዩ ታሪካዊና ፖለቲካዊ ውስብስብ ችግሮች ተተብትቦ እየዳከረ ያለ ፓርቲ መሆኑን የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡
በተጨማሪም ባለፉት ዓመታት በፓርቲው አመራሮቹ መካከል በተፈጠረ ልዩነትና ውዝግብ የፓርቲው ህልውና አበቃለት እስኪባል ድረስ የነበረውና አሁንም በያዝ ለቀቅ በፓርቲው ውስጥ የሚነሱት ወጀብና ዐውሎ ንፋሶች ዛሬም ድረስ ገና መፍትሔና መቋጫ ያገኙ አይመስሉም፡፡ የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው፣ ነፃነትን የማወጅ፣ ሉዓላዊነትን የማስከበር፣ የማንነት፣ የታሪክና ፖለቲካ ጥያቄ ነው፣ በማለት ጽንፈኛ አቋሙን በሚያራምደው ኦነግና ደጋፊዎቹ ዘንድ ዛሬም ድረስ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በሸዋው ንጉሥ በምኒልክ ሰይፍ ተቀጥቅጦ በአማራ ታሪክና ማንነት ላይ የተገነባ ነው የሚለው መከራከሪያቸው አሁንም ድረስ በአቋም ደረጃ በግልጽ የሚንጸባረቅ ነው፡፡
ወጣቱ የፖለቲካ ምሁርና ተንታኝ ጃዋር ሙሐመድም ይህንኑ ሐሳብ በመድገም እንዲህ ብሎአል፡- ‹‹ … ኢትዮጵያን የመሠረታት የሦስትዮሽ ጦርነት ግብግብ ነው፡፡ በአማራው፣ በኦሮሞው፣ በትግሬው ግብግብ ውስጥ ወደ መጨረሻ ላይ በአመራር ስር የበላይነቱን የያዘው አማራው ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ አሁን የምናያት ኢትዮጵያ ማንነቷ በአማራ ባሕላዊ ሥርጭትና  በአማራ ፖለቲካ የተገነባች ነች፡፡ … የኢትዮጵያ አገራዊ ማንነት የምንለውም የአማራ ባህላዊ ማንነት ነው፡፡›› ሲል ከኢትዮጵያ ታላቅ ሥልጣኔ፣ ታሪክና ከኢትዮጵያዊነት መንፈስ ወይም ማንነት ጋር የሚጣረስ ድምዳሜን ሰጥቶአል፡፡
ይህ ዓይነቱ ትንታኔ የኢትዮጵያን ታሪክ በአግባቡ ያለመረዳት ቀውስ ወይም ደግሞ ሆን ብሎ  የታሪክ እውነታን የማዛባት ዘመቻ ነው የሚመስለው፡፡ ኢትዮጵያ የምትባለው ምድርና ሕዝቦቿ ትናንትና ከመቶ ዓመት በፊት ምኒልክና ተከታዮቹ በኃይልና በሰይፍ በሚፈልጓት ቅርፅና ይዘት ቀጥቅጠው የፈጠሯት እንጂ የሚለው መከራከሪያ ሐሳብ በምንም መንገድ ውኃ ሊያነሳ የሚችል ሐሳብ አይመስለኝም፡፡ ይህ ዓይነቱ አመለካከት ከሺሕ ዓመታት በፊት ጀምሮ በገናና ሥልጣኔዋና ታሪኳ በዓለም መድረክ ስሟ ገኖ የወጣውን፣ ከአፍሪካ አልፎ በሰሜን አሜሪካና በካረቢያን በባርነትና በቅኝ ግዛት ቀንበር ስር ተይዘው ሲማቅቁ ለነበሩ ሕዝቦች የነፃነት ምድር፣ የጥቁር ሕዝቦች ተስፋ ‹‹የጥቁር ሕዝቦች የከነዓን ምድር›› በሚል በሰቀቀንና በናፍቆት ሲያስቧትና ሲዘክሯት የኖረችውን ኢትዮጵያን ህልውና የመካድ ያህል የሚቆጠር ይመስለኛል፡፡
ኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት መንፈስ የነፃነት ተምሳሌት፣ የአንድነትና የፍቅር ኪዳን ሆኖ በብዙዎች ልብ ውስጥ ሲንቀለቀልና ለዘመናት ሲያበራ የኖረ እውነት መሆኑን መካድ አንችልም፡፡ ከአፍሪካ አስከ አሜሪካ፣ ካረቢያና ጃማይካ ይህ ኢትዮጵያዊነት መንፈስ በእውቁ የነፃነት ታጋይ በእነ ማርከስ ጋርቬይ፣ በሬጌው ንጉሥ በእነ ቦብ ማርሌይ፣ በእነ ፒተር ቶሽ፣ በአፍሪካውያኑ የነፃነት አባቶች፣ በእነ ጆሞ ኬንያታ፣ በንኩርማ፣ በማንዴላና በበርካታ የነፃነት ታጋዮች ዘንድ የሞራልና ወኔ ስንቅ ሆኖ ያገለገለ፣ ክቡር ታሪክ፣ ሕያው አሻራና ቅርስ መሆኑን መዘንጋት ከታሪክ ሐቅ ጋር መጣላት ነው የሚሆነው፡፡
በተጨማሪም ለዚህችው በሺሕ ዘመናት ገናና ሥልጣኔዋ፣ ነፃነቷ፣ ታሪኳና ሉዓላዊነቷ ሲሉ በዐድዋ ጦር ግንባር ከወራሪው የአውሮጳ ኃይል ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ለሕዝቦቿም ነፃነት ዋጋ የከፈሉትን የኦሮሞ ተወላጆቹን የእነ ባልቻ አባ ነፍሶን፣ የእነ ደጃዝማች ገረሱ ዱኪን፣ የእነ ራስ አበበ አረጋይን፣ አውሮጳ ምድር ድረስ ዘልቆ በሮማ አደባባይ የኢትዮጵያውያንን አይበገሬነትና ለነፃነታቸው ቀናኢ ሕዝብ መሆናቸውን ያሳየውን የአብዲሳ አጋንና የበርካታ እልፍ የሚሆኑ የኦሮሞ ልጆችን ለሰው ልጆች ነፃነት የፈሰሰ ደምና መሥዋዕትነት ማራከስ ነው የሚሆነው፡፡
ከሰሞኑን የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩና አንጋፋው ፖለቲከኛ ፕ/ር መረራ ጉዲና፡- ‹‹የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የሕይወቴ ትዝታዎች፡- ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ እስከ ኢህአዴግ›› በሚል ርዕስ በጻፉት መጽሐፋቸውም በዓድዋው ጦርነት ከየትኛውም ሕዝብ ይልቅ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ጦር አዝማቾችና ጀግኖች ታላቅ መሥዋዕትነት መክፈላቸውን በመግለጽ የዓድዋ ድል የምኒልክን ቅኝ ግዛት ዘመቻ ያጠናከረ ዓውደ ግንባር ነው የሚለውን ሐሳብ አጣጥለው በመከራከር ጽፈዋል፡፡
በተጨማሪም ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ታላቅነትና አይበገሬነት በኦሎምፒክ መድረክ ከፍ ያደረጉ አበበ በቂላ፣ ዋሚ ቢራቱ፣ ቀነኒሳ በቀለ፣ ብርሃኔ አደሬ፣ ጌጤ ዋሚ፣ ጥሩነሽ ዲባባ፣ ፋጡማ ሮባ፣ ደራርቱ ቱሉ … እነዚህ ሁሉ በሮጡበት መድረክ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ብሔርና ሃይማኖት ሳይለዩ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ አብረው ሮጠዋል፣ ስለ ኢትዮጵያ ክብርና ድልም አብረው አምጠዋል፣ ተጨንቀዋል፡፡ በባርሴሎና ኦሎምፒክ መድረክ አበባችን ደራርቱ ቱሉ በአሥር ሺሕ ሜትር የመጀመሪያቱ አፍሪካዊት ሴት ወርቅ ሜዳሊስት በሆነችበት ድሏ የአገሯ ብሔራዊ መዝሙርና ሰንደቅ ዓላማ በስፔን ሰማይ ላይ ሲናኝና ከፍ ብሎ ሲታይ በጉንጯ ላይ ኮለል ብሎ የፈሰሰውን ዕንባዋን የታዘብን ሁሉ፣ በኢትዮጵያዊነት ኩራትና አይበገሬነት መንፈስ አብረናት በደስታ ሲቃ አንብተናል፣ መሬት ስመናል፡፡
ይህን ታሪክ በወርቅ ቀለም የጻፈውን የበርካታ ኦሮሞ ጀግኖችን ገድልና ለኢትዮጵያዊነት የተከፈለ መሥዋዕትነትን ማቃለልና ታሪክን ማዛባት ጤነኛ አካሄድ አይደለም፡፡ በዘመናችን ኦሮሙማን/የኦሮሞን ብሔርተኝነት በእጅጉ የሚሰብኩና የሚያራግቡ ሰዎች በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ ኦሮሙማን ወይም የኦሮሞ ብሔርተኝነነትን ለመገንባት ሲሉ የኢትዮጵያን የሺሕ ዘመናት ታሪክ፣ ሥልጣኔ፣ ቅርስና የኢትዮጵያዊነትን መንፈስ ማጣጣልና መንኳሰስ ጤነኛ አካሄድ አይመስለኝም፡፡
ኢትዮጵያዊነት እንደ ኮሶ ተበጥብጦ በግድ እያነገፈገፈን የተጋትነው፣ እየቀፈፈንና እየኮሰኮሰን የተደረበብን ማንነት ብለው ለሚከራከሩ ሰዎች በእርግጥም በግድ ሳይወዱ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ተቀበሉ ብሎ ማስገደድ እንደማይቻል አሳምሬ አውቃለሁ፡፡ ኢትዮጵያዊ ለመሆን ያለመፈለግ መብታቸውንም በግሌ አከብራለሁ፡፡ ይሁን እንጂ ታሪክን በማዛባት ጥቁር ሕዝቦች፣ መላው አፍሪካና በአጠቃላይ ነፃነትን አፍቃሪ የሆኑ ሕዝቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ዋጋና ክብር ያለውን የኢትዮጵያዊነትን መንፈስ ማራከስ፣ በኢትዮጵያና በሕዝቦቿን ታሪክ፣ ቅርስና ማንነት ላይ መዘባበት ጤነኛ አካሄድ እንዳልሆነ አሁንም በድጋሚ አስረግጬ ለመናገር እወዳለሁ፡፡

የአገር ውስጥ የደህንነት መምሪያ ሃላፊው አቶ ወልደሥላሴ ወልደሚካኤል በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ፤


esat

ፋና እንደዘገበው ፤ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋሉት የነበራቸውን ስልጣን ያለአባብ በመጠቀም ምንጩ ያልታወቀ ሃብት በማፍራት የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው ነው ።
ፋና ይህም ቢልም አቶ ወልደስላሴ -ከደህንነት ዋና ሹሙ ከአቶ ጌታቸው አሰፋ ጋር ጠብ ውስጥ ገብተው መቆየታቸው በስፋት ሲነገር ቆይቷል።
በተለይ መቀሌ በተካሄደው የህወሀት ጉባኤ ላይ በአቶ ጌታቸው አሰፋ እና በአቶ ወልደስላሴ መካከል ከፍተኛ ጭቅጭቅ ተፈጥሮ የነበረ ሲሆን፤በጉባኤው አቶ ወልደስላሴ-አቶ ጌታቸው አሰፋን “የአል አሙዲ ተላላኪ ሆኗል” እስከማለት ድረስ ዘልፈዋቸው ነበር።
በዚህም ሳቢያ የደህንነት ሹሙ አቶ ጌታቸው ቂም በመያዝና ከወራት በፊት በተደረገ ግምገማ አቶ ጌታቸውን ከሙስና ጋር በማያያዝ ከሀላፊነታቸው እንዲወገዱ አስደርገዋቸዋል።
ከወራት በፊት በዚህ መልኩ ከሀላፊነታቸው የተወገዱት አቶ ወልደሥላሴ ዛሬ በሙስና ክስ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከፌደራል ስነምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው ፥ ተጠርጣሪው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ቀርበው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል።
የዛሬ አመት ገደማ ኮሚሽኑ በአቶ ወልደስላሴ ወንበር ላይ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩትን አቶ አይቼው ተፈታን በተመሳሳይ ወንጀል ከሷቸው በአሁን ጊዜ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ እንደሆነም ፋና ጨምሮ ዘግቧል ።
አቶ ወልደስላሴ የህወሀት አባልና የትግራይ ልማት ማህበር የቦርድ አባል ናቸው።
ጸረ-ሙስና ኮሚሽን የውስጥ ተቀናቃኞችንና አፈንጋጮችን ማጥቂያ እንደሆነ ይታመናል።

ጓደኛውን በገጀራ ቆራርጦ የጣለው ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ነው


በተስፋሁን ብርሃኑ
ፖሊስና ርምጃው
‹‹እኔ ስራ አስገብቼው ሳለ ለአለቃዬ ዘወትር ስለ እኔ መጥፎ ነገር ይናገራል ያለውን ጓደኛውን ሶስት ቦታ ቆራርጦ የጣለው በፍርድ ቤት ጉዳዩ እየታየ ነው፡፡
ተጠርጣሪ ሀጎስ ገብሩና ሟች አምሳሉ ምትኩ በአራዳ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11/12 ልዩ ቦታው አራት ኪሎ ዩንቨርሳል ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ውስጥ በጥበቃ ስራ ላይ ተሰማርተው ይገኙ ነበር፡፡ ተጠርጣሪው ‹‹ዋና ፀባችን ነው ያለው እኔ ስራ አስገብቼው ልወደድ በማለት ዘወትር ስለ እኔ መጥፎ ነገር መናገርና እያመሸ እየመጣ ስራ ተበድሏል በማለት ያጣላኝ ነበር›› ብሏል፡፡ በምርመራ ወቅት፡፡ ይሄኔ ቂም የያዘው ተጠርጣሪ ሀጎስ ገብሩ ከሁለት ወር በፊት ለግድያ መዘጋጀት ይጀምራል፡፡
ለግድያ የሚያስፈልገውንም ከብረት የተሰራ ገጀራ ከመርካቶ እንደገዛ ተናግሯል፡፡ ሟች አምሳሉ ሲመጣ ‹‹እባክህ ራት በልቼ ልምጣ ስለው ባትበላ ምን አገባኝ አፈር ብላ ብሎኝ ወጣ›› ይላል ተጠርጣሪው በምርመራ ወቅት፡፡ ሟች በዚሁ ቀን አምሽቶ ሲመጣ በደሉ በዛብኝ ያለው ተጠርጣሪ በሩን ከከፈተለት በኋላ ሟችን በሩን እንዲዘጋው ከነገረው በኋላ ፊቱን ወደ በሩ ሲያዞር በያዘው ገጀራ ፊቱን ይመታዋል፡፡ ከዚያም ከመሬት ከወደቀ በኋላ አንገቱ አካባቢ ሲመታው ህይወቱ ሊያልፍ መቻሉ ተገልጿል፡፡
ተጠርጣሪው የሟችን አስክሬን ውሃ ወዳለበት ቦታ በመውሰድ በገጀራው ወገቡንና ሁለት እግሮቹን ቆራርጧል፡፡ ከወገብ በላይ አራት ኪሎ አካባቢ በሚገኝ ድልድይ መሻገሪያ ውስጥ የጣለው ሲሆን ግራና የቀኝ እግሩን ደግሞ በቢጫ ኩርቱ ፌስታል ጠቅልሎ የሚሰሩበት አካባቢና ብርሐንና ሰላም ማተሚያ ቤት ከፍ ብሎ በሚገኘው ሳጠራ ጠጅ ቤት አካባቢ ሊጥለው ችሏል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ የሰው መግደል ወንጀል መርማሪ ቡድን ወንጀሉ በተፈፀመ ሰሞን ከህብረተሰቡ ጋር በተደረገ ቅንጅት ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ሊያውሉት ችለዋል፡፡ መርማሪ ግሩም ታረቀኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ የግድያ ወንጀል መርማሪ አስፈላጊውን የሰውና የሰነድ ማሰረጃ አሰባሰበው ካጠናቀቁ በኋላ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት መዝገቡን ልከው ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

Thursday, August 29, 2013

ተስፋሁንን መግደል ለኢህአዴግ ተስፋ ይሆናታልን???? Abe tokichaw


bbbተስፋሁንን መግደል ለኢህአዴግ ተስፋ ይሆናታልን….!?
አብዲሳ የብዙ ጊዜ ወዳጄ ነበር፡፡ በየገጠሩ እየዞርን በርካታ ስራ አብረን ሰርተናል፡፡ የዋህነቱ እጅግ በጣም አስገራሚ ነበር፡፡ በየክልሉ ስንዞር አበሉን የሚጨርሰው “ቸገረኝ” ላለው ሁላ መበስጠት እንደነበር አብረነው የሰራ ሁላ እርሱን የምንለይበት ባህሪው ነው፡፡ ይሄ ልጅ በአንዱ ቀን ለስራ ልንሄድ የተቀጣጠርንበት ቦታ ሆነን ስንጠብቀው ስንጠብቀው ሳይመጣ ቀረ… ስልኩን ብንደውልልት አይሰራም፡፡ ካለንበት እየተንቆራጠጥን… ወደ ሶስት ሰዓት ድረስ ዘግይተን ጠበቅነው የውሃ ሸታ ሆነብን… ምን ሆነ ብለን እየተጨነቅን እንጀራ ነውና ጉዟችንን ቀጠልን…
አብረን ስንጓዝ ከነበርነው መካከል አብዲሳን በቅጡ የምናውቀው ሰዎች “ይሄኔ አንድ የታመ ሰው አጋጥሞት ሆስፒታል ሳላደርስ አልሄድም ብሎ ነው…” ….ወይ ደግሞ “…አንዱ ገንዘብ ተቸግሮ አጋጥሞት  ምንም ሳያስቀር ገንዘቡን ሰጥቶ ወደ እኛ መምጫ ራሱ ተቸግሮ ይሆናል …” ካልሆነ ግን “…ዘራፊዎች አግኝተው ጉድ አድርገውት ሊሆን ይችላል…. እያልን መገመታችንን ተያያዝነው…
ግምታችን ሁሉ ትክክል አልነበረም፡፡
አብዲሳ በስንተኛው ጊዜ በቴሌቪዥን መስኮት መታየቱን ሰማን… በየዋህነቱ የተቸገረ በመርዳቱ የምናውቀው አብዲ “አሸባሪ” ተብሎ በመንግስት ቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ አብዲሳ “አሻባሪ” ከተባለማ እኛ ምን ልንባል ነው… ብለን ራሳችንን እንደ ነውጠኛ የምናየው እኛ በጣም ተደነቅን!
አብዲ ወደ አምስት ወራት በማዕከላዊ፣ ወደ አምስት አመት በቃሊቲ እንዲሁም ሁለት ሶስት አመት ነው መሰለኝ በዝዋይ ማሰሪያ ቤቶች ቆይቶ ነፃ ነህ ተብሎ እስኪሰናበት ድረስ በአስር ቤቱ ውስጥ ሲደርስበት በነበረው መከራ ብዙ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ታድያ ከእስር ቤት ሊወጣ አካባቢ አንድ ባለስልጣን ብጤ ሰውዬ ጎብኝተውት ነበር፡፡
እስር ቤቱ እንዴት ነበር… ሲሉ ጠየቁት፡፡ አብዲሳ ምን አላቸው መሰልዎ… እስር ቤቱ እንዴት እንደሆነ ራስዎት ገብተው ካላዩት በስተቀር እንዲህ ነው ብዬ  ብነግሮት አይገባዎትም ፡፡ አላቸው፡፡
ይሄው ሰሞኑን ወንድማችን ተስፋሁን ጫመዳ በእስር ቤት በደረሰበት ስቃይ የተነሳ ህይወቱ ማለፏን ሰማን፡፡ ተስፋሁን በ1999 ዓ.ም መንግስት ኬኒያ ድረስ አፍኖ ወሳጆቹን ልኮ ለኬኒያ ፖሊስ ሽልጉን ከፍሎ፤ (የኬኒያ ፖሊስ እንኳንስ ከፍለውት እንዲሁም ጤዛ ነው) ብቻ በትብብር ወደ አዲስ አበባ ተወስዶ ነበር… ከዛም በታሰረበት ሆኖ ሞተን ሰማን!
ለዚህ ጉዳይ የሚሰማ ቢኖር የኬኒያን መንግስት ራሱ ፍርድ ቤት ማቆም የሚገባ ይመስለኛል፡፡
ፍርድ ቤት ሳይቀርብ ራሱ፤ በነፍስ ማጥፋት ወንጀል እግዜሩም እኛም የምንጠይቀው ግን የገዛ መንግስታችን ነው፡፡ አዎ መንግስታችን እጁ ላይ የተለያዩ ሀገራት ብድር ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ሰዎች እምባ የተለያዩ ሰዎች ደምም አለበት፡፡
ተስፋሁን ለምን እንዲሞት ተፈረደበት… እውን ለሀገሪቱ ደህንነት ስጋት ሆኖ ነውን… የሚለውን በፍጹም!!! ለማለት፤ እነ አብዲሳን ያየነው እኛ ምስክሮች ነን፡፡ ምስኪኑ አብዲሳ ስምንት አመት ታስሮ በነፃ ከመፈታቱ በፊት “የሀገር ስጋት ሽብርተኛ!” ተብሎ ነበር የታሰረው፡፡  በእስር ቤት የደረሰበትን ስቃይ ሰው ሆኖ መፈጠርን የሚያስጠላ ነው፡፡ የነገረኝን በሙሉ ለማሳየት በፊልም እንጂ ጽሁፍ የሚገልፀው አይደለም፡፡
እሺ ኢንጂነር ተስፋሁን የኦነግ ወይም የሌላ ተቃዋሚ አባል ወይም ደጋፊ ወይም እንዳሻቸው ይሁኑ ባይ ነው እንበለው፡፡ ግን እርሱን በመግደል የሚቃወሙ ሰዎችን ተስፋ ማስቆረጥ አልያም  ቁጥራቸውን መቀነስ ይቻላል….
ኢህአዴግ በጫካ እያለች ታጋዮቿ እና ሰላዮቿ ደርግ በቁጥጥር ስር ሲያውላቸው ቀጥታ አብዮታዊ እርምጃ ይወስድባቸው ነበር፡፡ ውጤቱ ግን ምንድነው  የሆነው… ብለው የጠየቁ እንደሆ፤  ውጤቱ ብሶቱን እያጠነከረው ቁጭቱን እያባሰው እምቢ ባይነቱን እያበረታው ነው የሄደው…!
ዛሬ ቁጥር ስፍር የሌላቸው ኢትዮጵያውያን በእስር ቤት ውስጥ ፍዳቸውን እያዩ ነው… የምር ለኢህአዴግ እናስባለን የምትሉ ሰዎች የእነ ተስፋሁን ግድያ የኢህአዴግ ተስፋ ሟጠጡን ያሳያልና…. ይሄ ነገር መሞቻሽ ነው ብላችሁ ምከሯት፡፡ እምቢ ካለች ግን መከራው ይመክራታል፡፡
ምክር!
ባለስልጣኖቻችን ሆይ እናንተ ማረሚያ ቤት የምትሏቸው እስር ቤቶች መግደያ ቤት እየሆኑ ነው፡፡ ብልጥ ከሆናችሁ…. አብዲሳ እንዳለው ራሳችሁ ገብታችሁ ሳታዩት በፊት በእስር ለሚማቅቁ ወገኖቻችን መላ ፈልጉ!
ተስፋሁን ጫመዳ ነፍሱን ከደህናው ስፍራ ያሳርፍልን! ለቤተሰቦቹም መጸናናትን ይስጥልን!

የእሁዱ ሰልፍን ሳንሰላስለው...........Abe tokichaw



21

እንኳንስ ሌላው ቀርቶ፤ አዲስ አበባ ስታድየም የከተማው ደርቢ እግር ኳስ ጨዋታ ሲኖር የቡና ልጆች ሚስማር የሳንጃው ልጆች ደግሞ ዳፍ ነው የሚገቡት፡፡ ጥላ ፎቁንም ግራ እና ቀኝ ብለው ይካፈሉታል፡፡
ይህንን የሚያደርጉት ሁለቱም ቡድኖቻቸው በአንድ ሜዳ ስለሚጫወቱ ማዶ ለማዶ ሆነው መሀል ላይ የሚጫወተውን ቡድናቸውን ለማበረታታት ነው፡፡ እንጂ ለብሽሽቅ ብለው አይቀጣጠሩም… ኳስ ጨዋታ በሌለበት እስቲ እናንተም ውጡ እኛም እንውጣ እና እናደበላልቀው ብለው ሲጠራሩ ሰምቼ አላውቅም፡፡
ነሀሴ 26 በመስቀል አደባባይ ሁለት ሰልፎች ተጠርተዋል፡፡ አንደኛው ሰማያዊ ፓርቲ ከሶስት ወር በፊት ላደረገው ሰልፍ ምላሽ ካላገኘሁ እመለስበታለሁ ብሎ ሲዘጋጅበት የከረመው ሲሆን፤ ሌላው ደግሞ ድንገት ከየት መጣ ከየት ሳንለው የተከሰተው የሀይማኖት ተቋማት የጠሩት ሰልፍ ነው፡፡ ይህ ሰልፍ በተዘዋዋሪ መንግስታችን የጠራው ሰልፍ መሆኑን ያወቅነው ቤት ለቤት እየቀሰቀሱ ያሉትን ቀበሌ ቀበሌ የሚጫወቱ ሴቶች ከማየታችን በፊት በኢቲቪ ዜና አንባቢው ጮክ ብሎ ሲናገር የሰማን ጊዜ ነው፡፡
እሁድ ነሀሴ 26 መንግስት፤ ተቀናቃኙ ሰማያዊ ፓርቲ ቀድሞ በጠራው ሰልፍ ላይ ሌላ ሰልፍ መጥራቱ ባስበው ባስበው አሁንም ባሰበው ምክንያቱ አልገለፅልህ ብሎኛል፡፡
ሰልፍን ደጋግሜ ሳንሰላስለው ሳንሰላስለው…. መንግስታችን ኢህአዴግ ይህንን ሰልፍ ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ቀን ላይ ደርቦ ሲጠራ እንደው በደረቁ ሰልፍ ብሎ ከሚጠራ ለሰማያዊ ፓርቲ ሰዎች አንዳች ሆነ ግብዣ ቢያደርግ እና…
መሀል መስቀል አደባባይ ከሁለቱም ወገን የሚገኙ አመራሮች የሚሳተፉበት አይደል ሾው ነገር ወይም ደግሞ ድሮ ጊዜ እንደሚደረገው ሁለቱም ወገኖች አሉ የሚሏቸውን አዋቂዎቻቸውን አቁመው ርስ በርስ የሚሟገቱበት እና በህዝቡ ዘንድ የሀሳብ ብልጫ ለመያዝ ሙከራ የሚያደርጉበት የክርክር ውድድር ካልሆነ ካልሆነ ደግሞ የሆነ የቁንጅና ወድድር ነገር ቢያሳዩን ብዬ በማሰብ ላይ እገኛለሁ… ሸግዬ አሳብ አይደለም ትላላችሁ…!
የምር ግን ኢህአዴግ የጠራው ሰልፍ የምሩን ነው ማለት ነው…
እኔ የምለው የሀይማኖት ተቋማቱ መንግስት ይሄንን እንዲያደርጉ ሲያዛቸው ዝም ብለው እሺ ከሚሉት ሰብሰብ ብለው ፀልየው ከህመሙ እንዲፈወስ ቢያደርጉልን ምናለ… እውነቴን ነው ምላችሁ መንግስቴ ታሟል!
Abe Tokicha
w

Dr. King’s Dream: An Ethiopian’s Perspective


By Tewodros Abebe
August 28, 2013





Although I was familiar with the name Martin Luther King Jr. during my teenage years in Ethiopia, I never had a full understanding of the man’s fascinating story or the level of his greatness. That understanding came during my undergraduate years at an American college.
As a young student who had always been interested in the art of writing, I decided to take as many literature courses as I possibly could. One course focused on styles of composition. One of the textbooks assigned for that particular course introduced readers to different writing styles and genres of the English language. I enjoyed every single essay in that book, but one stood out: “Letter from a Birmingham Jail” by Dr. King.
I still remember the stunning effect his 1963 letter had on me as I read it for the first time. It was an eye-opening document that illustrated the suffering, humiliation and struggle that African Americans had to endure in order to attain justice, equality and civil rights. I never knew!
The letter and its sobering contents were simply captivating. I felt like it was addressed to me and, at the same time, to every individual in every part of the world. I never anticipated that I would identify with his message so closely and with such intensity. The letter prompted me to reflect on the chronic political turmoil and persecutions in my own country and in many African nations. It provoked me to ponder on the grimness of life for African children and the unspeakable human rights violations that governments commit against their own people. It compelled me to think, solemnly, of my fellow Africans’ and the continent’s seemingly inseparable fate with poverty and injustice, which are the direct consequences of bad policies and corrupt leadership. Nevertheless, I tried to maintain an optimistic outlook as Dr. King did in the closing remarks of his extraordinary letter:

Let us all hope that the dark clouds of racial prejudice will soon pass away and the deep fog of misunderstanding will be lifted from our fear drenched communities, and in some not too distant tomorrow the radiant stars of love and brotherhood will shine over our great nation with all their scintillating beauty.
Dr. King’s eloquent remarks should serve as cautionary words to a world that chooses to focus on differences rather than the fundamental similarities of the human race.
The letter that introduced me to his writings inspired me to read more about Dr. King and his brilliant leadership in the civil rights movement. The speech that transformed American
society, which was delivered on Aug. 28, 1963, at the Lincoln Memorial in Washington, D.C., remains my favorite: “I Have a Dream.” It is simply one of the most important, thoughtful and emotionally stirring speeches of modern times. Just like his Birmingham letter, “I Have a Dream” also has a universal appeal that speaks truth to people of every nationality. Every time I watch the video of the speech or read its text, I am reminded of the necessity to speak against injustices around the world. It is a highly inspiring speech that gives tremendous hope to all people who are languishing under the brutal rules of wicked oppressors and ruthless dictators.
As we observe the fiftieth anniversary of the “dream” speech and the historic March on Washington this year, we must continue to be mindful of the human understanding and connection that Dr. King strived to nurture throughout his life. Like all great world leaders, the powerful message that he successfully transmitted through his writings and speeches is applicable today, and to all people. Let us recognize the fact that, with faith and determination, people around the world, to use his own words, “will be able to transform the jangling discords” of their nations “into a beautiful symphony of brotherhood.”

Dr. King had a phenomenal dream. As citizens of the world, let’s work on ours collectively.

የእኛ “መንግስት” (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)


August 29, 2013
“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም” ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1 ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤ ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡J
እናም የስርዓቱን የአስተዳደር ዘይቤ ያለፍርሃት አደባባይ ካዋልነው የቀድሞ ገዥዎቻችን የተጓዙበትን ጎዳና እየተከተለ መሆኑን ለመተንተን የምሁራንን ጥናት መጠበቅ ግድ አይለም፤ ምክንያቱም ለዓመታት የተመለከትነው እውነታ የሚነግረን የአመራሩን እና በዙሪያው የሠፈሩ የጥቅም ተጋሪ ግለሰቦችን ብልፅግና ታሳቢ ያደረገ፣ ከታግሎ መጣል ህግ የተቀዳ፣ የራስ ሀገርንና የራስ ሕዝብን በምርኮ ያስገበረ ፖለቲካ መንበሩን ነው፤ ገብር፣ ገብር፣ ገብር…!!
ዛሬ መንገድ ዳር ረሀብ አዙሮ የጣለው ወንድምህ ስቃይ እንደ ጥላ የሚከተልህ፤ ህፃናት በትምህርት ገበታቸው ላይ በጠኔ ተሸንፈው መመልከቱ የሰርክ አሳዛኝ ክስተት የሆነብህ ከሰው ሰራሽ ችጋር፣ ከሰው ሰራሽ የቀዬ ፍንቀላ፣ ከሰው ሰራሽ እርዛት… የመነጨ መርገምት እንጂ የሰማይ ቁጣ አይምሰልህ፤ እመነኝ መለስም ሆነ ተተኪዎቹ ስኬት አድርገው የሚሰብኩትም ይህንን ነው፤ ‹ሀገር አቀናን!› የሚሉትም ይህንን ነው፤ ሰሞኑን የሚያሰለቹህ ተረኛ ምሁራንም ‹‹ትምህርትና ጤናን በተመለከተ መለስ ‹እልል› የሚያስብል ሥራ ሰርቷል›› የሚሉህ ጣራና ግድግዳ እየቆጠሩ ነው፤ ይህ አይነቱ መደዴ ሙገሳም ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ሪፖርት ለማዘጋጀት ከሚረዳ ቁጥር የዘለለ አበርክቶ አንደማይኖረው አትዘንጋ፡፡
እውነት እውነት እልሀለሁ፡- ይህ የሆነበት ብቸኛው ምክንያት መንግስት በስልጣን ላይ ስለሚቆይበትመንገድ ብቻ መጨነቅን ግዴታው በማድረጉ ነው፤ ይህንን ለመረዳትም እያገባደድን ባለው ክረምት የመንግስት ትኩረት በምን ላይ አንደሆነ የሚያሳይ ማስረጃን ጨርፌ ላሳይህ፡፡
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የእስልምና እምነት ተከታዮች መንግስት በሃይማኖታቸው ጣልቃ መግባቱን በመቃወም እና የታሰሩ ኮሚቴዎቻቸው እንዲፈቱ በመጠየቅ እያደረጉ ያለውን ትግል በሰላማዊ መንገድ አጠንክረው ሲቀጥሉ፤በተቃራኒው ‹‹ፀጥታ አስከባሪዎች›› አንዳንዴ በጥይት፣ አንዳንዴ በአስለቃሽ ጢስ፣ አንዳንዴ በማጋዝ…ምላሽ ሲሰጡ…
በርግጥ መንግስት ከኃይል እርምጃው በተጨማሪ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎችን (በምን አግባብቶ ወይም በምን አስፈራርቶ እንደሆነ ባይታወቅም) ወደ አደባባይ በማስወጣት መብት ጠያቂዎቹን ከ‹‹አክራሪ››ነት እና ‹‹ወሃቢዝም››ነት ጋር አያይዘው የውግዘት በረዶ እንዲያዘንቡባቸው እያደረገ ነው፡፡ ኢቲቪም ይህንን ኩነት እየተከታተለ ማራገቡን ቀጥሎበታል፤ ‹‹የቲፒ ከተማ ነዋሪዎች ‹አክራሪዎችን አወገዙ››፤ ‹‹በደቡብ ወሎ ኩታ በር ዞን አንድነት ፓርቲ ህገ-ወጥ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰልፍ ተካሄደ››፤ ‹‹የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ‹የሼሁ ግድያ ድራማ አይደለም› አሉ፣ ‹የሼህ ኑሩ ኢልም ነው፣ የአሸባሪዎች ብር ነውም›ብለዋል››፤‹‹የመርሀቤቴ ነዋሪዎች ፅንፈኞችን በመቃወም የአቋም መግለጫ አወጡ››፤…
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- አንድነት ፓርቲ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የ‹‹ፀረ-ሽብር ሕጉ›› እንዲሰረዝና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ እና የአዳራሽ ስብሰባዎችን እያካሄደ ነው፤ መንግስትም አንዳንዴ የአፀፋ የድጋፍ ሰልፍ ሲያካሄድ፤አንዳንዴ የአዳራሽ ስብሰባዎች ከመካሄዳቸው አስቀድሞ ‹መጋኛ› ሲሆንባቸው፤ አንዳንዴም የአስተባባሪዎቹን መኪና ጎማ ሲያፈነዳ፤ አንዳንዴም አዳራሽ ከልክሎ ሲያደናቅፋቸው… መዋሉ ፋታ የነሳው ይመስላል፤ በወላይታ የተጠራውን የአዳራሽ ስብሰባም ‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ የትውልድ ቦታ እንዴት ተደርጎ!›› ያሉ ካድሬዎች የአንድነት ሰዎችን አዋክበው ስብሰባውን አክሽፈዋል፤
ክረምቱእንዲህእየተገባደደነው፡-ገዥው ፓርቲ ‹የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ አንደኛ ሙት ዓመት አከብራለሁ› በሚል መላ ኢትዮጵያን ችግኝ መትከያ፣ መላ ዜጎቿን ደግሞ ወደ አርሶ አደርነት በአስማት የቀየራቸው አስመስሏቸዋል፤ቴሊቪዥንና ራዲዮንም አስፈላጊነታቸው በየመንደሩ ችግኝ መተከሉን እየተከታተሉ መዘገብ ብቻ እስኪመስል ድረስ እንዲህ ሲሉ ጀምበር ወጥታ ትጠልቃለች፡- ‹‹የላይ አርማጮህ ነዋሪዎች ችግኝ ተከሉ››፣ ‹‹በመቀሌ ከተማ ‹ዘመቻ መለስ› በሚል የችግኝ ተከላ ተካሄደ››፣ ‹‹አቃቂ ኮረብታ ላይ በሚሊዮን የሚቆጠር ችግኝ በኦሮሚያ ፌደራል ፖሊስ አባላት ተተከለ፤ ቦታውም ‹መለስዜናዊ ኮረብታ› ተብሎ ተሰይሟል››፣ ‹‹በምዕራብ ሀረርጌ አስራ ሰባት ሚሊዮን፣ በወልበራ አስራ አራት ሚሊዮን ችግኝተ ተክሏል››፣ ‹‹በመንዝ ላሎ ወረዳ ተቆጥሮ የማያልቅ ችግኝ ተከላ ተደርጓል››፣ ‹‹የብአዴን አመራርና ካድሬ በባህር ዳር ከተማ በቢሊዮን የሚቆጠር ችግኝ ተከሉ፤ በፕሮግራሙ ላይ ጓድ አዲሱ ለገሰ ‹ችግኝ የምንተክለው አገሪቱ በአረንጓዴው ልማት በአለማችን ማግኘት የሚገባትን ቦታ እንድታገኝ ለማድረግ ነው› ሲል፣ ጓድ በረከት ስምዖን ደግሞ ‹ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአለማችን በአንድ ጊዜ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ችግኝ እየተከሉ ያሉባት ብቸኛ ሀገር ናት› ብሏል››፤‹‹ዝክረ መለስ 1ኛ ዓመት መታሰቢያን ምክንያት በማድረግ ከሐምሌ አስራ አምስት ቀን ጀምሮ ሁሉም ቀበሌዎች በስሙ ‹ፓርክ› ሰይመው ችግኝ ተከላ እያካሄዱ›› መሆኑን ደግሞ የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ መግለፁን የአማራ ክልል ብዙሃን መገናኛ ዘግቧል፤ ‹‹በወልቂጤ ከተማ በተደረገው ችግኝ ተከላ ላይም አንዲት ወጣት ‹መለስ ለሴቶች የተለየ አመለካከት ነበረው›› ማለቷም በዘገባው ተጠቅሷል፤ …ማን ነበር የመለስ ራዕይ ‹ችግኝ መትከል ነው› ያለው? …ኢህአዴግ ይሆን?
ከዚሁ ጎን ለጎን (አሁንም ሙት ዓመቱን ለማሰብ) በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የእግር ጉዞ ተደርጓል፣ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓትም ተካሄዷል፤መነሻውን መቀሌ፣ መድረሻውን አዲስ አበባ ያደረገ ‹‹የመለስ ቱር አረንጓዴ ልማት›› የብስክሌት ውድድርም ሊጠናቀቅ ገና አንድ ሳምንት ይቀረዋል፤ በብሄራዊና ሀይማኖታዊ በዓላት ቀንለሃያ አንድ ጊዜ ይሰማ የነበረው የመድፍ ድምፅም፣ የመለስን አንደኛ ሙት ዓመት ለማብሰር ተተኩሷል፤ …በግድ አልቅሱ፣ በግድ ተዝካር አውጡ፣ በግድ ችግኝ ትከሉ፣ በግድ ተወያዩ፣ በግድ አደባባይ ውጡ፣ በግድ የፎቶ ግራፍ ኤግዚቢሽን ጎብኙ፣ በግድ.. ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ሽፈራው ሽጉጤ ከአንድ ሺህ ሰባት መቶ በላይ ለሚሆኑ የዩኒቨርስቲ ከፍተኛ መምህራን ‹የአቅም ግንባታ ስልጠና› እየሰጡ ነው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምሁራኖቹን ማሰልጠን ያስፈለገበት ምክንያት ‹‹ብቃት ያለው ምርጥ የተማረ ኃይል ለማፍራት››መሆኑን ቢነግርህ አይግረምህ፤ ይህ ኢትዮጵያ ነውና የዐዋቂነት ማረጋገጫው መማር፣ ማንበብ፣ መመራመር… አይደለም፣ የፖለቲካውን ኃይል መያዝ እንጂ፤ ‹ስልጣን ላለው ሁሉምሚስጥረ-ጥበብይገለፅለታል› እንዲል አብዮታዊ ዲሞክራሲ መለስ ዜናዊም በሁሉም መስክ ‹አስተማሪ› ነበር፤ የህግ ባለሙያዎችን ሰብስቦ የሀገሪቱን ወንጀለኛ መቅጫ ህግ ትርጓሜ ሲተነትን ደጋግመህ ሰምተኸዋል፤ በቀጣዩ ቀን ደግሞ ለግብርና ባለሙያዎች ከውሃ ማቆር እስከ በላብራቶሪ የሚዳቀል ምርጥ ዘር ድረስ ባሉጉዳዮችዙሪያ የሁለት ቀን ማብራሪያ መስጠቱን ታስታውሳለህ፤ እመነኝ ተተኪው ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህንኑ ነው እያደረገ ያለው፤ የሆነ ሆኖ ኃ/ማርያም ለምሁራኖች ከሙያቸው ጋር ስለተያያዙ ጉዳዮች ጭምር በሰጣቸው ስልጠና ላይ እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀርቦለት ነበር ‹‹የኢንዱስትሪዎች በበቂ ሁኔታ አለመኖሩ፣ በክፍል ውስጥ የምናስተምረውን ንድፈ ሃሳብ በተግባር ለማሳየት እንቅፋት ሆኖብናል››፤ በርግጥጠቅላይ ሚንስትሩ‹‹መፍትሄ››ያለውን የተናገረው ብዙም ሳይጨነቅ ‹‹እኔ ኢንዱስትሪን ‹ዲፋይን› የማደርገው ግብርናም ኢንዱስትሪ ነው ብዬ ነው››በማለት ነበር፤…ግና!ይህ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በተጨባጭ አላብራራም፡፡ለምሳሌ ህክምና የሚያጠና ተማሪ በምን መልኩ በሞፈርና ቀንበር የተግባር ልምምድ ማድረግ እንደሚችል፤ወይም ፖለቲካ ሳይንስ የሚያጠና ተማሪ የተግባር ልምምዱን በግብርና ኢንዱስትሪ እንዴት ሊወጣው እንደሚችል? ማለቴ ነው፡፡
ለዓመታት በርካታ ምሁራን ብቃት አልባ ተማሪዎች እንደ ሰማይ ከዋክብት የመብዛታቸው መንስኤን ከትምህርት ፖለሲው ጋር የሚያነፃፅሩበትን ሀቲት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ ባገኘው የሀገር መሪነት ስልጣን ገልብጦ በዩንቨርስቲ ቆይታው መምህራኖቹ የነበሩትንም ጭምር ‹‹አቅም አንሷችኋልና-እገነባችኋለሁ›› ሲል ከመስማት የከፋ እንደ ሀገር ክሽፈት የለም (በነገራችን ላይ ከወራት በፊት ለኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በረከት ስምዖን፣ ቴውድሮስ አዳህኖም፣ ሶፍያን አህመድ በአጠቃላይ ሁሉም የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት አንድ ህንዳዊ ፕሮፌሰር በኢህአዴግ ጽ/ቤት ‹‹ልማታዊ መንግስት›› እንዴት ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል ሲተነትንላቸው፣ እነርሱም ደብተርና እስክርቢቶ ይዘው በንቃት ሲከታተሉ የቴሌቪዥ ዋና ዜና ሆኖ የቀረበበትን ምክንያት ዛሬም ድረስ ሊገለፅልኝ አልቻለም፤ በተለይም ፕሮፈሰር እንድርያስ እሸቴ ‹‹በቃሉ የፀና…›› በሚል ርዕስ መለስን አስመልክቶ በተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም ላይ ‹‹በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ ልማታዊ ስርዓተ መንግስት ‹ዴሞክራሲያዊ ሊሆን ይችላል፤ መሆንም አለበት› ብሎ በአደባባይ የተከራከረው እኔ እስከማውቀው ድረስ መለስ ነበር›› ማለቱን፣ ተተኪዎቹ ፍልስፍናውን ገና እየተማሩት ከመሆኑ አንፃር ስናየውሀገራችን ያለችበት ሁኔታ ጉዞው ወዴት ነው? ያስብላል፡፡ …ከቶስ በተማሪ ፖለቲከኛ የሚተዳደር ሕዝብ ከኢትዮጵያ በቀር ወዴት ይኖራል?)
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የህዳሴውን ግድብ ከዳር ለማድረስ በቂ ገንዘብ ስላልተገኘ ተደጋጋሚ የቦንድ ሽያጭ እየተካሄደ ነው፤ አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞችም በካድሬ ባልደረቦቻቸው ጫና በድጋሚ ቦንድ ለመግዛት መወሰናቸው ተሰምቷል፤ በርግጥ ከፍተኛ የኢህአዴግ የአመራር አባላት በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ቦንድ እንዲገዙ ለመቀስቀስ የአዘጋጇቸው ስብሰባዎች ‹‹ቅድሚያ የዜጎች መብት ይከበር›› ባሉ የሀገራችን ልጆች መክሸፉም የክረምቱ የመንግስት ዋና ሥራ ነው፤ ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- በነቢብ የኢትዮጵያ፣ በገቢር የገዥው ፓርቲ የግል ንብረት የሆነው ቴሌቪዥን ጣቢያ ባለፉት ሶስት ወር ብቻ ከሃያ በላይ ‹‹ዶክመንተሪ ፊልም›› አሳይቷል (ገና ይቀጥላልም) በርዕሳቸው እንደሚከተለው እንዘርዝራቸው፡- ‹‹ኢፍቲን›› በሶማሊያ ላይ የሚያጠነጥን፣ ‹‹የጥቁር ህዝቦች ልሳን (መለስ በአፍሪካ)››፣ ‹‹ከፓን አፍሪካ እስከ አፍሪካ ህዳሴ›› የጠቅላይ ሚንስትር መለስን ህይወት የሚዳስስ፣ ‹‹ዘመነ አፍሪካ››፣ ‹‹የአፍሪካ ልሳን-መለስ››፣ ‹‹መለስ ማን ነው?››፣ ‹‹ሀገሬ-ቤቴ››፣ ‹‹ባለራዕዮቹ›› ስራ ፈጠራ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ደውል›› እና ‹‹ደውል 2›› ህገወጥ-የሰዎች ዝውውርን በተመለከተ (በተለያያ ጊዜ የተላለፉ)፣ ‹‹የዲያስፖራ የልማት እንቅስቃሴ››፣ የካርታ ስራ ድርጅትን በተመለከተ፣ ‹‹የጥልቅ አስተሳሰብ ባለቤት›› በፕ/ር እንድርያስ እሸቴ ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥን፣ ምድር ባቡር ኮርፕሬሽንን በተመለከተ፣ ‹‹ያልተለመደ ጉብኝት›› የአዲስ አበባ አስተዳደር የአምስት ዓመት የመንግስት ግንባታዎችን በተመለከተ፣ ‹‹ሼህ ኑር ለምን ሞቱ?›› የደሴውን ሼህ ኑር ይማምን ግድያ በተመለከተ፣ ‹‹የተስፋ ስንቅ››፣‹‹በቃሉ የፀና›› በድህረ መለስ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ያልተጠኑ ገፆች›› በመለስ ዜናዊ ህይወት ዙሪያ (በርግጥ በዚህ ፊልም እህቱ ጠላ፣ ወንድሙ አንባሻ በመሸጥ መተዳደራቸውን በምስልም በድምፅም ማቅረቡ ምን የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ እንደሆነ ለማወቅ ግራ ያጋባል፤ …ምናልባት እንዲያ እየዘረፈ ለቤተሰቦቹ ‹ሶልዲን› የማይሰጥ ‹ቆነቋና› ነበር ለማለት ይሆን? ወይስ ለአዜብ መስፍን ‹የወር ቀለባችንን እንቸገራለን› የአንድ ሰሞን ማስተዛዘኛ ምስክር ፍለጋ ነው?
በጥቅሉ ለኢህአዴግ ሕዝብን የማስተዳደር፣ ሀገርን የመምራት መገለጫ ይህ ነው፤ ሌላ አይደለም፤ ግና! ለዘመናት ያልተመለሱ ጥያቄዎቻችን ዛሬም መጮኻቸውን አላቋረጡምና እነሆ እንዲህ ቀጥለዋል፡- ሀገር ማስተዳደር ‹መለስ ጀግና ነበር› እያሉ ማሰልቸት ነውን? የመንግስትስ ስራ (ግዴታ) ምንድር ነው? ሀገሪቱን ‹‹መለስ-ፓርክ›› ወደሚል ስያሜ ከመቀየራችሁ በፊት፣ ለጤፍ ዋጋ አለቅጥ መናር ምክንያቱን ስለምን መመርመር ተሳናቸው? ሀገሪቱን በ‹አራጣ› እንደያዘ ስግብግብ ነጋዴ በሚሊዮኖች ህይወት ላይ የማይሞላ ‹ሳፋ› ደቅኖ አዋጣ፣ ግዛ፣ ክፈል፣ ገብር… እያለ የሚያስጨንቀው ማን ነው? ስለመለስ ‹የሃሳብ ምጡቅነት› መስካሪ ምሁራኖቻችን ለጎዳና ኑሮ የተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ስንት ሚሊዮን እንደደረሱ እና እልፍ አላፍት ታዳጊዎቻችን በሴተኛ አዳሪነት እንደተሰማሩ የምትነግሩን መቼ ነው?እንዲህ የመሆኑ ምክንያትስ በማን ይሆን? ‹የሁለት ዲጂቱ›ዕድገት ሸክምን የማለዘብ አቅም ከሌለውፋይዳው ምንድር ነው? ‹ሳቅ ትዝታ› ስለሆነባቸው ጎጆዎች ለምን አትነግሩንም? መለስ ‹ያለመለማት› ኢትዮጵያ ወዴት ትሆን? ‹ፖለቲካ› ማለትስ ይህ ነውን? …ነጋ ድራስ ገ/ህይወት እንዳሉት ‹‹…መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡›› የመተራረሚያው ጊዜም በጣም ያለፈ ይመስለኛል፡፡ አገዛዙን ‹እንደ መንግስት› መቀበሉም እንዲሁ፡፡

የሕወሐት ባለስልጣናት የአሜሪካ ቆይታ፤ የከዱ አሉ


946847_524794230895033_334002608_n
August 29, 2013
ከኢየሩሳሌም አርአያ
በአባይ ወልዱ የሚመራውና ሰባት ከፍተኛ የሕወሐት ባለስልጣናት የተካተቱበት ቡድን በአሜሪካ አራት ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ በተለይ በላስቬጋስ ጠንካራ ተቃውሞ እንደገጠመው በስፍራው የተገኙ ምንጮች አስታወቁ። ቡድኑ በዋሽንግተን ኢትዮጲያ ኤምባሲ በጀመረውና በመቀጠል በላስቬጋስ፣ ሲያትልና ካሊፎርኒያ ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ “አላማ” አድርጎ የያዛቸው ጉዳዮች እንደነበሩ የጠቆሙት ምንጮች፣ እነሱም፥ “የመለስ ፋውንዴሽን፣ የአባይ ግድብና የ40/60 የቤቶች ግንባታ.” ሲሆኑ፣ ለነዚህ ማስፈፀሚያ “ገንዘብ አዋጡ” የሚለው ዋናው ግብ እንደነበር አስረድተዋል። በተለይ ደግሞ « በትግራይ ተወላጁ ዘንድ ሕወሐት የለም፣ ተከፋፍሏል፣ ተዳክሟል፣ ፓርቲው ሰው የለውም፤» የሚለውን እራሱ ቡድኑ በማንሳት ለገዛ ጥያቄው መልስ ሲሰጥ « ሕወሐት አሁንም ሃይል አለው፤ አልተዳከመም» በማለት አድራጊ- ፈጣሪ በመሆን ስልጣኑን በበላይነት ተቆጣጥሮ እንደያዘና ቡድኑ የመጣውም “አይዟችሁ” ለማለት እንደሆነ መገለፁን በቅርብ የተከታተሉት ምንጮች አስታውቀዋል። ቡድኑ በተጨማሪም ፥ « ልማት አልምተናል፤ ትግራይ እየለማ ነው፤ ህዝቡን ተጠቃሚ እያደረገነው ነው» ከማለቱ ባሻገር « በትግራይ ተወላጁ ላይ አደጋ ተደቅኗል፤ የሙስሊሙ፣ የትምክህተኞችና የሽብርተኞች አደገኛ እንቅስቃሴ እያንዣበበ መሆኑን፣…የተደቀነብህን አደጋ ከጎናችን ሆነህ ተከላከል፤ ያለበለዚያ ግን ሊያጠፉህ ነው፤» ሲሉ መናገራቸውን የገለፁት ምንጮች አክለውም፣ « አባላት የሆናችሁ ተወደደም ተጠላ መሬትና መኖሪያ ቤት እንሰጣችኋለን፤ ለዚህም ከእኛ ጎን መሰለፍ አለባችሁ» በማለት ሊሸነግሉ መሞከራቸውን ጠቁመዋል።
ከዋሽንግተን ስብሰባ (ለሁለት ተከፍሎ ነው የተካሄደው) በኋላ ወደ ሶስቱ ከተሞች ተከፋፍለው እንደሄዱ ሲታወቅ፥ ሲያትል አቶ ብርሃነ ማረት፣ እንዲሁም ላስቬስጋስ አባይ ወልዱና ተክለወይኒ አሰፋ መሄዳቸው ታውቋል። በተለይ በላስቬጋስ ጠንካራ ተቃውሞ የገጠማቸው እነአባይ ስብሰባው ከቀኑ 2፡00 ሰዓት ይጀመራል ተብሎ ከአራት ሰዓት በኋላ ዘግይቶ አመሻሽ ላይ መጀመሩን ምንጮች ገልፀዋል። ስብሰባው ሲጀመር ከላይ የተገለፁትን ጉዳዮች ያደመጠው ተሰብሳቢ ተከታዮቹን ጥያቄ አቀረበ፤ « ዴሞክራሲ አለ ትላላችሁ፣ ነገር ግን ዴሞክራሲ የለም፤ በሃሳብ የሚቃወማችሁን ታስራላችሁ፣ ታንገላታላችሁ፣ የሰብአዊ መብት ረገጣ ታካሂዳላችሁ፤ ከእናንተ የተለየ ሃሳብ ያለውን ትፈራላችሁ፤ ለምንድነው ይህን ሁሉ የምታደርጉት?….በማ.ረ.ት.(ማህበር ረድኤት ትግራይ) በትግራይ ሕዝብ ስም የምትሰበስቡትን ገንዘብ ለአራጣ ብድር እና ለፖለቲካ መጠቀሚያ በመሳሪያነት እያዋላችሁት ነው። ለምን?….ትእምት (ኤፈርት) ማነው ባለቤቱ?..በማን ነው የሚመራው?..ማነው የሚቆጣጠረው?..ለመሆኑ ኦዲት ተደርጎ ያውቃል ወይ?..እነማናቸው እየተጠቀሙበት ያለው?» የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ጥያቄዎች እንደነበሩ ምንጮቹ የጠቆሙ ሲሆን፣ አባይ ወልዱ « እኔ አልመልስም፣ ተ/ወይኒ መልስ ይስጥበት» ቢሉም ነገር ግን ግልፅና አግባብ ያለው ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ወደ ማመናጨቅና ቁጣ ያመሩት ተ/ወይኒ በዚህ ድርጊታቸው በርካታ ተሰብሳቢዎችን እንዳሳዘኑ አስረድተዋል። በዚህ የተበሳጨው ተሰብሳቢ « ጥያቄያችን አልተመለሰም» በማለቱና ሁከትና ያለመደማመጥ በማየሉ ስብሰባው እንዲቋረጥ መደረጉን የጠቆሙት ምንጮች፣ የጥያቄና ተቃውሞው መብዛት ያስደነገጣቸው ባለስልጣናቱ የመረጡት ማምለጫ በላስቬጋስ ተወካያቸው በሆነውና መድረክ ሲመራ በነበረው አቶ ተወልደ በኩል፥ « አዳራሹን የተከራየንበት ሰአት አብቅቷል፤ ስለዚህም ስብሰባው አብቅቷል » በማለት በአስቂኝ ሰበብ መቋረጡን አያይዘው ገልፀዋል። እነአባይ ከአዳራሹ ሲወጡ ቀድሞ ውጭ ሆኖ ይጠብቃቸው በነበረው ተሰብሳቢ ውግዘትና ስድብ እንደደረሰባቸው ያስታወቁት ምንጮች « ሌባ..ሌባ…ሙሰኞች..» የሚሉ ተቃውሞዎች ጎላ ብለው እንደተሰሙ አመልክተዋል።
ስብሰባዎቹን የታዘቡ ወገኖች በሰጡት አስተያየት እንዲህ ብለዋል፤ « በአንድ በኩል ልማት እያካሄድን ነው፤ እያሉና ገንዘብ እየጠየቁ በሌላ በኩል “ትግራዋይ አደጋ ተደቅኖብሃል፣ ከጎናችን ሆነህ ተከላከል፤” ማለት እርስ በርሱ የሚጋጭና ድጋፍ የማግኛ የፖለቲካ የፖለቲካ ቁማር ነው። ያልተጠየቁትን የፓርቲውን ህልውና (ስለ ሕወሐት) አንስቶ መነገሩም አስገራሚና አጠያያቂ ነው።» ሲሉ ትዝብታቸውን የጀመሩት እነዚህ ወገኖች በማያያዝም፥ « እነዚህ ሰባት ባለስልጣናት ወደ አሜሪካ የመጡት ከነዘመዶቻቸው፣ ጋሻ ጃግሬዎቻቸው ሲሆን፣ ባለስልጣናቱ የመንግስት ወኪሎች እንደመሆናቸው – በማን ገንዝብ ነው የሚንቀሳቀሱት?..የሚለው መጠየቅ አለበት። በሕዝብ ገንዝብ እየተንፈላሰሱ እንደሆነ ግልፅ ነው። የትግራይ ተወላጁን ብቻ ለይተው ስብሰባ የሚጠሩት ለምንድነው?…በእርግጥ ስላሰቡለት ነው?…የሚሉት ሲፈተሹ .መልሱ በጭራሽ አይደለም ነው። አላማቸውና ትኩረት የሰጡት የትግራይ ተወላጁን እየተንከባከቡት እንደሆነና ተጠቃሚ መሆኑን ለማሳየት በመፈለግ፣ እግረ-መንገዳቸውን ከቀሪው ኢትዮጲያዊ ወገኑ ጋር በመነጠል..ድጋፍ ለማግኘትና በውስጣቸው የተፈጠረውን ቀውስ በዚህ በኩል ቀዳዳውን ለመድፈን የሚደረግ የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ስልት ነው። ..ደግሞስ ሕወሐት “አጋር” ከሚላቸው ብ.አ.ዴ.ን፣ ኦ.ህ.ዴ.ድ.፣ ደቡብ ሕዝቦች ተለይቶ፣ በሕዝብ ገንዘብ ስብሰባ የሚጠራበትና ያሻውን የሚያደርግበት አግባብ ምንድነው?..የሚለው ከዚህ ጋር መታየት ያለብት ነው። ፖለቲካዊ ፍጆታና ማንአለብኝነት በፓርቲው በመነገሱ እንደሆነ ደግሞ ግልፅ ነው።» ብለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፥ አሜሪካ ከመጡት ሰባት የሕወሐት ባለስልጣናት መካከል- ማለትም አባይ ወልዱ፣ ብርሃነ ኪ/ማሪያም፣ ተ/ወይኒ አሰፋና ዳንኤል አሰፋ በዋነኛነት ሲጠቀሱ፣ ከሰባቱ ሶስቱ ስብሰባውን ሳያካሂዱ ከቡድኑ ተገንጥለው በአሜሪካ መቅረታቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል። ቤተሰቦቻቸውን ይዘው (ልጆቻቸውን ጭምር) በመምጣት አሜሪካ ጥገኝነት ጠይቀው መቅረትን የመረጡት ባለስልጣናት ውስጥ የሕወሐት ማ/ኮሚቴ አባላት እንዳሉ ያረጋገጡት ምንጮች በቅርቡ ዝርዝሩን ይፋ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

Wednesday, August 28, 2013

የወያኔ መንግስት የግንቦት 7 ቡድን አባላት ናቸው ብሎ የጠረጠራቸው ላይ ክስ መሰረተ


የግንቦት 7 አሸባሪ ቡድን አባላት ናቸው በሚል የተጠረጠሩ 10 ግለሰቦች ክስ ተመሰረተባቸው ።
ተከሳሾቹ ዘመኑ ካሳ በዕውቄ የግንቦት ሰባት ልዩ ሃይል ታጣቂ ፣ አሸናፊ አካሉ አበራ ፣ ደህናሁን ቤዛ ስመኝ ፣ ምንዳዬ ለማ ፣ አንሙት የኔዋስ አለኽኝ ፣ሳለኝ አሰፋ ወንድምአገኝ ፣ የአማራ ክልል የማረሚያ ቤት ረዳት ሽፍት መሪ ምክትል ኢንስፔክተር ሙሉዬ ማናዬ ረታ፣ፀጋው ካሳ እንየው ፣ የአለም አካሉ አበራ እና ሙሉ ሲሳይ መቆያ የተባሉ ተጠርጣሪዎች  ናቸው ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት  ከፈረጀውና እራሱን ግንቦት ሰባት እያለ ከሚጠራው ድርጅት አመራሮች ጋር በመገናኘት ለሽብር ስር በጋራ ተንቀሳቅሰዋል በሚል ነው  የፌዴራሉ አቃቤ ህግ ክስ የመሰረተባቸው ።
የፌዴራሉ አቃቤ ህግ መረጃዎችን ሰብስቦ ነሃሴ 13 ክስ መስርቶባቸው ትላንት በአቃቂ ጊዜያዊ 4ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡ ሲሆን፤ተከሳሾቹ ጠበቃ የማቆም አቅም ስለሌላቸው የመንግስት ጠበቃ እንዲቆምላቸው ችሎቱ አዟል።
ችሎቱ  1ኛ ተከሳሽ በሌለበት ክሱ በመቅረቡ በጋዜጣ እንዲጠራ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ክሱን ለመስማትም  ችሎቱ ለህዳር 2 ቀን  2006 ዓመተ ምህረት ቀጠሮ ይዟል ።

Tuesday, August 27, 2013

ከወራት በፊት ለኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በረከት ስምዖን፣ የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በህንዳዊ ፕሮፌሰር ሲማሩ ነበር(ተመስገን ደሳለኝ)



“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም” ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1 ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤ ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡
እናም የስርዓቱን የአስተዳደር ዘይቤ ያለፍርሃት አደባባይ ካዋልነው የቀድሞ ገዥዎቻችን የተጓዙበትን ጎዳና እየተከተለ መሆኑን ለመተንተን የምሁራንን ጥናት መጠበቅ ግድ አይለም፤ ምክንያቱም ለዓመታት የተመለከትነው እውነታ የሚነግረን የአመራሩን እና በዙሪያው የሠፈሩ የጥቅም ተጋሪ ግለሰቦችን ብልፅግና ታሳቢ ያደረገ፣ ከታግሎ መጣል ህግ የተቀዳ፣ የራስ ሀገርንና የራስ ሕዝብን በምርኮ ያስገበረ ፖለቲካ መንበሩን ነው፤ ገብር፣ ገብር፣ ገብር…!!
ዛሬ መንገድ ዳር ረሀብ አዙሮ የጣለው ወንድምህ ስቃይ እንደ ጥላ የሚከተልህ፤ ህፃናት በትምህርት ገበታቸው ላይ በጠኔ ተሸንፈው መመልከቱ የሰርክ አሳዛኝ ክስተት የሆነብህ ከሰው ሰራሽ ችጋር፣ ከሰው ሰራሽ የቀዬ ፍንቀላ፣ ከሰው ሰራሽ እርዛት… የመነጨ መርገምት እንጂ የሰማይ ቁጣ አይምሰልህ፤ እመነኝ መለስም ሆነ ተተኪዎቹ ስኬት አድርገው የሚሰብኩትም ይህንን ነው፤ ‹ሀገር አቀናን!› የሚሉትም ይህንን ነው፤ ሰሞኑን የሚያሰለቹህ ተረኛ ምሁራንም ‹‹ትምህርትና ጤናን በተመለከተ መለስ ‹እልል› የሚያስብል ሥራ ሰርቷል›› የሚሉህ ጣራና ግድግዳ እየቆጠሩ ነው፤ ይህ አይነቱ መደዴ ሙገሳም ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ሪፖርት ለማዘጋጀት ከሚረዳ ቁጥር የዘለለ አበርክቶ አንደማይኖረው አትዘንጋ፡፡
እውነት እውነት እልሀለሁ፡- ይህ የሆነበት ብቸኛው ምክንያት መንግስት በስልጣን ላይ ስለሚቆይበትመንገድ ብቻ መጨነቅን ግዴታው በማድረጉ ነው፤ ይህንን ለመረዳትም እያገባደድን ባለው ክረምት የመንግስት ትኩረት በምን ላይ አንደሆነ የሚያሳይ ማስረጃን ጨርፌ ላሳይህ፡፡
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የእስልምና እምነት ተከታዮች መንግስት በሃይማኖታቸው ጣልቃ መግባቱን በመቃወም እና የታሰሩ ኮሚቴዎቻቸው እንዲፈቱ በመጠየቅ እያደረጉ ያለውን ትግል በሰላማዊ መንገድ አጠንክረው ሲቀጥሉ፤በተቃራኒው ‹‹ፀጥታ አስከባሪዎች›› አንዳንዴ በጥይት፣ አንዳንዴ በአስለቃሽ ጢስ፣ አንዳንዴ በማጋዝ…ምላሽ ሲሰጡ…
በርግጥ መንግስት ከኃይል እርምጃው በተጨማሪ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎችን (በምን አግባብቶ ወይም በምን አስፈራርቶ እንደሆነ ባይታወቅም) ወደ አደባባይ በማስወጣት መብት ጠያቂዎቹን ከ‹‹አክራሪ››ነት እና ‹‹ወሃቢዝም››ነት ጋር አያይዘው የውግዘት በረዶ እንዲያዘንቡባቸው እያደረገ ነው፡፡ ኢቲቪም ይህንን ኩነት እየተከታተለ ማራገቡን ቀጥሎበታል፤ ‹‹የቲፒ ከተማ ነዋሪዎች ‹አክራሪዎችን አወገዙ››፤ ‹‹በደቡብ ወሎ ኩታ በር ዞን አንድነት ፓርቲ ህገ-ወጥ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰልፍ ተካሄደ››፤ ‹‹የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ‹የሼሁ ግድያ ድራማ አይደለም› አሉ፣ ‹የሼህ ኑሩ ኢልም ነው፣ የአሸባሪዎች ብር ነውም›ብለዋል››፤‹‹የመርሀቤቴ ነዋሪዎች ፅንፈኞችን በመቃወም የአቋም መግለጫ አወጡ››፤…
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- አንድነት ፓርቲ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የ‹‹ፀረ-ሽብር ሕጉ›› እንዲሰረዝና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ እና የአዳራሽ ስብሰባዎችን እያካሄደ ነው፤ መንግስትም አንዳንዴ የአፀፋ የድጋፍ ሰልፍ ሲያካሄድ፤አንዳንዴ የአዳራሽ ስብሰባዎች ከመካሄዳቸው አስቀድሞ ‹መጋኛ› ሲሆንባቸው፤ አንዳንዴም የአስተባባሪዎቹን መኪና ጎማ ሲያፈነዳ፤ አንዳንዴም አዳራሽ ከልክሎ ሲያደናቅፋቸው… መዋሉ ፋታ የነሳው ይመስላል፤ በወላይታ የተጠራውን የአዳራሽ ስብሰባም ‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ የትውልድ ቦታ እንዴት ተደርጎ!›› ያሉ ካድሬዎች የአንድነት ሰዎችን አዋክበው ስብሰባውን አክሽፈዋል፤ ክረምቱእንዲህእየተገባደደነው፡-ገዥው ፓርቲ ‹የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ አንደኛ ሙት ዓመት አከብራለሁ› በሚል መላ ኢትዮጵያን ችግኝ መትከያ፣ መላ ዜጎቿን ደግሞ ወደ አርሶ አደርነት በአስማት የቀየራቸው አስመስሏቸዋል፤ቴሊቪዥንና ራዲዮንም አስፈላጊነታቸው በየመንደሩ ችግኝ መተከሉን እየተከታተሉ መዘገብ ብቻ እስኪመስል ድረስ እንዲህ ሲሉ ጀምበር ወጥታ ትጠልቃለች፡- ‹‹የላይ አርማጮህ ነዋሪዎች ችግኝ ተከሉ››፣ ‹‹በመቀሌ ከተማ ‹ዘመቻ መለስ› በሚል የችግኝ ተከላ ተካሄደ››፣ ‹‹አቃቂ ኮረብታ ላይ በሚሊዮን የሚቆጠር ችግኝ በኦሮሚያ ፌደራል ፖሊስ አባላት ተተከለ፤ ቦታውም ‹መለስዜናዊ ኮረብታ› ተብሎ ተሰይሟል››፣ ‹‹በምዕራብ ሀረርጌ አስራ ሰባት ሚሊዮን፣ በወልበራ አስራ አራት ሚሊዮን ችግኝተ ተክሏል››፣ ‹‹በመንዝ ላሎ ወረዳ ተቆጥሮ የማያልቅ ችግኝ ተከላ ተደርጓል››፣ ‹‹የብአዴን አመራርና ካድሬ በባህር ዳር ከተማ በቢሊዮን የሚቆጠር ችግኝ ተከሉ፤ በፕሮግራሙ ላይ ጓድ አዲሱ ለገሰ ‹ችግኝ የምንተክለው አገሪቱ በአረንጓዴው ልማት በአለማችን ማግኘት የሚገባትን ቦታ እንድታገኝ ለማድረግ ነው› ሲል፣ ተመስገን ደሳለኝጓድ በረከት ስምዖን ደግሞ ‹ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአለማችን በአንድ ጊዜ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ችግኝ እየተከሉ ያሉባት ብቸኛ ሀገር ናት› ብሏል››፤‹‹ዝክረ መለስ 1ኛ ዓመት መታሰቢያን ምክንያት በማድረግ ከሐምሌ አስራ አምስት ቀን ጀምሮ ሁሉም ቀበሌዎች በስሙ ‹ፓርክ› ሰይመው ችግኝ ተከላ እያካሄዱ›› መሆኑን ደግሞ የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ መግለፁን የአማራ ክልል ብዙሃን መገናኛ ዘግቧል፤ ‹‹በወልቂጤ ከተማ በተደረገው ችግኝ ተከላ ላይም አንዲት ወጣት ‹መለስ ለሴቶች የተለየ አመለካከት ነበረው›› ማለቷም በዘገባው ተጠቅሷል፤ …ማን ነበር የመለስ ራዕይ ‹ችግኝ መትከል ነው› ያለው? …ኢህአዴግ ይሆን?
ከዚሁ ጎን ለጎን (አሁንም ሙት ዓመቱን ለማሰብ) በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የእግር ጉዞ ተደርጓል፣ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓትም ተካሄዷል፤መነሻውን መቀሌ፣ መድረሻውን አዲስ አበባ ያደረገ ‹‹የመለስ ቱር አረንጓዴ ልማት›› የብስክሌት ውድድርም ሊጠናቀቅ ገና አንድ ሳምንት ይቀረዋል፤ በብሄራዊና ሀይማኖታዊ በዓላት ቀንለሃያ አንድ ጊዜ ይሰማ የነበረው የመድፍ ድምፅም፣ የመለስን አንደኛ ሙት ዓመት ለማብሰር ተተኩሷል፤ …በግድ አልቅሱ፣ በግድ ተዝካር አውጡ፣ በግድ ችግኝ ትከሉ፣ በግድ ተወያዩ፣ በግድ አደባባይ ውጡ፣ በግድ የፎቶ ግራፍ ኤግዚቢሽን ጎብኙ፣ በግድ..
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ሽፈራው ሽጉጤ ከአንድ ሺህ ሰባት መቶ በላይ ለሚሆኑ የዩኒቨርስቲ ከፍተኛ መምህራን ‹የአቅም ግንባታ ስልጠና› እየሰጡ ነው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምሁራኖቹን ማሰልጠን ያስፈለገበት ምክንያት ‹‹ብቃት ያለው ምርጥ የተማረ ኃይል ለማፍራት››መሆኑን ቢነግርህ አይግረምህ፤ ይህ ኢትዮጵያ ነውና የዐዋቂነት ማረጋገጫው መማር፣ ማንበብ፣ መመራመር… አይደለም፣ የፖለቲካውን ኃይል መያዝ እንጂ፤ ‹ስልጣን ላለው ሁሉምሚስጥረ-ጥበብይገለፅለታል› እንዲል አብዮታዊ ዲሞክራሲ መለስ ዜናዊም በሁሉም መስክ ‹አስተማሪ› ነበር፤ የህግ ባለሙያዎችን ሰብስቦ የሀገሪቱን ወንጀለኛ መቅጫ ህግ ትርጓሜ ሲተነትን ደጋግመህ ሰምተኸዋል፤ በቀጣዩ ቀን ደግሞ ለግብርና ባለሙያዎች ከውሃ ማቆር እስከ በላብራቶሪ የሚዳቀል ምርጥ ዘር ድረስ ባሉጉዳዮችዙሪያ የሁለት ቀን ማብራሪያ መስጠቱን ታስታውሳለህ፤ እመነኝ ተተኪው ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህንኑ ነው እያደረገ ያለው፤
የሆነ ሆኖ ኃ/ማርያም ለምሁራኖች ከሙያቸው ጋር ስለተያያዙ ጉዳዮች ጭምር በሰጣቸው ስልጠና ላይ እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀርቦለት ነበር ‹‹የኢንዱስትሪዎች በበቂ ሁኔታ አለመኖሩ፣ በክፍል ውስጥ የምናስተምረውን ንድፈ ሃሳብ በተግባር ለማሳየት እንቅፋት ሆኖብናል››፤ በርግጥጠቅላይ ሚንስትሩ‹‹መፍትሄ››ያለውን የተናገረው ብዙም ሳይጨነቅ ‹‹እኔ ኢንዱስትሪን ‹ዲፋይን› የማደርገው ግብርናም ኢንዱስትሪ ነው ብዬ ነው››በማለት ነበር፤…ግና!ይህ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በተጨባጭ አላብራራም፡፡ ለምሳሌ ህክምና የሚያጠና ተማሪ በምን መልኩ በሞፈርና ቀንበር የተግባር ልምምድ ማድረግ እንደሚችል፤ወይም ፖለቲካ ሳይንስ የሚያጠና ተማሪ የተግባር ልምምዱን በግብርና ኢንዱስትሪ እንዴት ሊወጣው እንደሚችል? ማለቴ ነው፡፡
ለዓመታት በርካታ ምሁራን ብቃት አልባ ተማሪዎች እንደ ሰማይ ከዋክብት የመብዛታቸው መንስኤን ከትምህርት ፖለሲው ጋር የሚያነፃፅሩበትን ሀቲት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ ባገኘው የሀገር መሪነት ስልጣን ገልብጦ በዩንቨርስቲ ቆይታው መምህራኖቹ የነበሩትንም ጭምር ‹‹አቅም አንሷችኋልና-እገነባችኋለሁ›› ሲል ከመስማት የከፋ እንደ ሀገር ክሽፈት የለም (በነገራችን ላይ ከወራት በፊት ለኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በረከት ስምዖን፣ ቴውድሮስ አዳህኖም፣ ሶፍያን አህመድ በአጠቃላይ ሁሉም የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት አንድ ህንዳዊ ፕሮፌሰር በኢህአዴግ ጽ/ቤት ‹‹ልማታዊ መንግስት›› እንዴት ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል ሲተነትንላቸው፣ እነርሱም ደብተርና እስክርቢቶ ይዘው በንቃት ሲከታተሉ የቴሌቪዥ ዋና ዜና ሆኖ የቀረበበትን ምክንያት ዛሬም ድረስ ሊገለፅልኝ አልቻለም፤ በተለይም ፕሮፈሰር እንድርያስ እሸቴ ‹‹በቃሉ የፀና…›› በሚል ርዕስ መለስን አስመልክቶ በተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም ላይ ‹‹በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ ልማታዊ ስርዓተ መንግስት ‹ዴሞክራሲያዊ ሊሆን ይችላል፤ መሆንም አለበት› ብሎ በአደባባይ የተከራከረው እኔ እስከማውቀው ድረስ መለስ ነበር›› ማለቱን፣ ተተኪዎቹ ፍልስፍናውን ገና እየተማሩት ከመሆኑ አንፃር ስናየውሀገራችን ያለችበት ሁኔታ ጉዞው ወዴት ነው? ያስብላል፡፡ …ከቶስ በተማሪ ፖለቲከኛ የሚተዳደር ሕዝብ ከኢትዮጵያ በቀር ወዴት ይኖራል?)
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የህዳሴውን ግድብ ከዳር ለማድረስ በቂ ገንዘብ ስላልተገኘ ተደጋጋሚ የቦንድ ሽያጭ እየተካሄደ ነው፤ አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞችም በካድሬ ባልደረቦቻቸው ጫና በድጋሚ ቦንድ ለመግዛት መወሰናቸው ተሰምቷል፤ በርግጥ ከፍተኛ የኢህአዴግ የአመራር አባላት በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ቦንድ እንዲገዙ ለመቀስቀስ የአዘጋጇቸው ስብሰባዎች ‹‹ቅድሚያ የዜጎች መብት ይከበር›› ባሉ የሀገራችን ልጆች መክሸፉም የክረምቱ የመንግስት ዋና ሥራ ነው፤
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- በነቢብ የኢትዮጵያ፣ በገቢር የገዥው ፓርቲ የግል ንብረት የሆነው ቴሌቪዥን ጣቢያ ባለፉት ሶስት ወር ብቻ ከሃያ በላይ ‹‹ዶክመንተሪ ፊልም›› አሳይቷል (ገና ይቀጥላልም) በርዕሳቸው እንደሚከተለው እንዘርዝራቸው፡- ‹‹ኢፍቲን›› በሶማሊያ ላይ የሚያጠነጥን፣ ‹‹የጥቁር ህዝቦች ልሳን (መለስ በአፍሪካ)››፣ ‹‹ከፓን አፍሪካ እስከ አፍሪካ ህዳሴ›› የጠቅላይ ሚንስትር መለስን ህይወት የሚዳስስ፣ ‹‹ዘመነ አፍሪካ››፣ ‹‹የአፍሪካ ልሳን-መለስ››፣ ‹‹መለስ ማን ነው?››፣ ‹‹ሀገሬ-ቤቴ››፣ ‹‹ባለራዕዮቹ›› ስራ ፈጠራ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ደውል›› እና ‹‹ደውል 2›› ህገወጥ-የሰዎች ዝውውርን በተመለከተ (በተለያያ ጊዜ የተላለፉ)፣ ‹‹የዲያስፖራ የልማት እንቅስቃሴ››፣ የካርታ ስራ ድርጅትን በተመለከተ፣ ‹‹የጥልቅ አስተሳሰብ ባለቤት›› በፕ/ር እንድርያስ እሸቴ ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥን፣ ምድር ባቡር ኮርፕሬሽንን በተመለከተ፣ ‹‹ያልተለመደ ጉብኝት›› የአዲስ አበባ አስተዳደር የአምስት ዓመት የመንግስት ግንባታዎችን በተመለከተ፣ ‹‹ሼህ ኑር ለምን ሞቱ?›› የደሴውን ሼህ ኑር ይማምን ግድያ በተመለከተ፣ ‹‹የተስፋ ስንቅ››፣‹‹በቃሉ የፀና›› በድህረ መለስ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ያልተጠኑ ገፆች›› በመለስ ዜናዊ ህይወት ዙሪያ (በርግጥ በዚህ ፊልም እህቱ ጠላ፣ ወንድሙ አንባሻ በመሸጥ መተዳደራቸውን በምስልም በድምፅም ማቅረቡ ምን የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ እንደሆነ ለማወቅ ግራ ያጋባል፤ …ምናልባትእንዲያ እየዘረፈ ለቤተሰቦቹ ‹ሶልዲን› የማይሰጥ ‹ቆነቋና› ነበር ለማለት ይሆን? ወይስ ለአዜብ መስፍን ‹የወር ቀለባችንን እንቸገራለን› የአንድ ሰሞን ማስተዛዘኛ ምስክር ፍለጋ ነው?
በጥቅሉ ለኢህአዴግ ሕዝብን የማስተዳደር፣ ሀገርን የመምራት መገለጫ ይህ ነው፤ ሌላ አይደለም፤ ግና! ለዘመናት ያልተመለሱ ጥያቄዎቻችን ዛሬም መጮኻቸውን አላቋረጡምና እነሆ እንዲህ ቀጥለዋል፡- ሀገር ማስተዳደር ‹መለስ ጀግና ነበር› እያሉ ማሰልቸት ነውን? የመንግስትስ ስራ (ግዴታ) ምንድር ነው? ሀገሪቱን ‹‹መለስ-ፓርክ›› ወደሚል ስያሜ ከመቀየራችሁ በፊት፣ ለጤፍ ዋጋ አለቅጥ መናር ምክንያቱን ስለምን መመርመር ተሳናቸው? ሀገሪቱን በ‹አራጣ› እንደያዘ ስግብግብ ነጋዴ በሚሊዮኖች ህይወት ላይ የማይሞላ ‹ሳፋ› ደቅኖ አዋጣ፣ ግዛ፣ ክፈል፣ ገብር… እያለ የሚያስጨንቀው ማን ነው? ስለመለስ ‹የሃሳብ ምጡቅነት› መስካሪ ምሁራኖቻችን ለጎዳና ኑሮ የተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ስንት ሚሊዮን እንደደረሱ እና እልፍ አላፍት ታዳጊዎቻችን በሴተኛ አዳሪነት እንደተሰማሩ የምትነግሩን መቼ ነው?እንዲህ የመሆኑ ምክንያትስ በማን ይሆን? ‹የሁለት ዲጂቱ›ዕድገት ሸክምን የማለዘብ አቅም ከሌለውፋይዳው ምንድር ነው? ‹ሳቅ ትዝታ› ስለሆነባቸው ጎጆዎች ለምን አትነግሩንም? መለስ ‹ያለመለማት› ኢትዮጵያ ወዴት ትሆን? ‹ፖለቲካ› ማለትስ ይህ ነውን?…ነጋ ድራስ ገ/ህይወት እንዳሉት ‹‹…መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡›› የመተራረሚያው ጊዜም በጣም ያለፈ ይመስለኛል፡፡ አገዛዙን ‹እንደ መንግስት› መቀበሉም እንዲሁ፡፡